🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ያስመዘገበችው የ11 ቢሊየን ዶላር የወጪ ንግድ ገቢ፣ ሀገሪቱ ከ1984 እስከ 2000 ዓ.ም ባሉት 17 ተከታታይ ዓመታት ውስጥ ካገኘችው አጠቃላይ የኤክስፖርት ገቢ ጋር እኩል መሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው፣ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፤ ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ያስመዘገበችው የ11 ቢሊየን ዶላር የወጪ ንግድ ገቢ፣ ሀገሪቱ ከ1984 እስከ 2000 ዓ.ም ባሉት 17 ተከታታይ ዓመታት ውስጥ በድምሩ ካገኘችው አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ ጋር እኩል መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ ከዕቅዱ በላይ አፈጻጸም የታየበትና በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው ታላቅ ውጤት የኢትዮጵያውያን የጋራ ድል መሆኑንም ተናግረዋል።
የውጭ ምንዛሬ ገቢ ምንጮችን በዝርዝር ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከአገልግሎት ወጪ ንግድ 9 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር፣ ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት 4 ቢሊየን ዶላር ገደማ፣ እንዲሁም ከሬሚታንስ 7 ነጥብ 9 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም ከእርዳታና ብድር 5 ቢሊየን ዶላር ገደማ ወደ ሀገር ውስጥ ፈሰስ መደረጉን ጠቁመው፤ በአጠቃላይ ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 38 ቢሊየን ዶላር ገደማ የውጭ ካፒታል ፍሰት ማግኘቷን አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 8, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 4, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...
Jun 17, 2026