🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ያስመዘገበችው የ11 ቢሊየን ዶላር የወጪ ንግድ ገቢ፣ ሀገሪቱ ከ1984 እስከ 2000 ዓ.ም ባሉት 17 ተከታታይ ዓመታት ውስጥ ካገኘችው አጠቃላይ የኤክስፖርት ገቢ ጋር እኩል መሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው፣ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፤ ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ያስመዘገበችው የ11 ቢሊየን ዶላር የወጪ ንግድ ገቢ፣ ሀገሪቱ ከ1984 እስከ 2000 ዓ.ም ባሉት 17 ተከታታይ ዓመታት ውስጥ በድምሩ ካገኘችው አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ ጋር እኩል መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ ከዕቅዱ በላይ አፈጻጸም የታየበትና በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው ታላቅ ውጤት የኢትዮጵያውያን የጋራ ድል መሆኑንም ተናግረዋል።
የውጭ ምንዛሬ ገቢ ምንጮችን በዝርዝር ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከአገልግሎት ወጪ ንግድ 9 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር፣ ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት 4 ቢሊየን ዶላር ገደማ፣ እንዲሁም ከሬሚታንስ 7 ነጥብ 9 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም ከእርዳታና ብድር 5 ቢሊየን ዶላር ገደማ ወደ ሀገር ውስጥ ፈሰስ መደረጉን ጠቁመው፤ በአጠቃላይ ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 38 ቢሊየን ዶላር ገደማ የውጭ ካፒታል ፍሰት ማግኘቷን አስታውቀዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026