🔇Unmute
ቡታጅራ፤ ሰኔ 30/2018 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሃላፊ ቀመሪያ ረሻድ የቢሮውን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫን በማስመልከት ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።
በክልሉ ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ በተሰራው ሥራ ውጤት መገኘቱንና ይህንንም አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በ2018 በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መቻሉንም አስታውቀዋል።
የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ9 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።
በቀጣይም የግብር አሰባሰብ ሥራውን ለማሳካት የግብር ህጉን የማስከበርና ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎች በተከታታይነት እንደሚሰሩ አንስተዋል።
በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሂደትንና ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስረድተዋል።
በዚህም ክልሉ በ2019 በጀት ዓመት ከ33 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ለመሰብሰብ መታቀዱን ያነሱት ሃላፊዋ፣ ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ግብሩን በታማኝነት በመክፈል ሃላፊነቱን እንዲወጣም አስገንዝበዋል።
በክልሉ የሚገኙ ከ115 ሺህ 790 በላይ የደረጃ የ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል ለክልሉ ልማት መጠናከር የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንዲያጠናክሩም ጠይቀዋል።
የገቢ አሰባሳብ ስርዓቱን በማዘመን ቀልጣፋና ፈጣን የገቢ አሰራርን ተግባራዊ መደረጉን ያነሱት ሃላፊዋ፣ ግብር ከፋዮችም የጊዜና ጉልበት ብክነትን በሚታደጉ የቴክኖሎጂ አማራጮች ተጠቅመው ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ አስገንዝበዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 8, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 4, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...
Jun 17, 2026