የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቡታጅራ፤ ሰኔ 30/2018 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ሃላፊ ቀመሪያ ረሻድ የቢሮውን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫን በማስመልከት ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

በክልሉ ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ በተሰራው ሥራ ውጤት መገኘቱንና ይህንንም አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በ2018 በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መቻሉንም አስታውቀዋል።

የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ9 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።

በቀጣይም የግብር አሰባሰብ ሥራውን ለማሳካት የግብር ህጉን የማስከበርና ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎች በተከታታይነት እንደሚሰሩ አንስተዋል።

በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሂደትንና ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስረድተዋል።

በዚህም ክልሉ በ2019 በጀት ዓመት ከ33 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ለመሰብሰብ መታቀዱን ያነሱት ሃላፊዋ፣ ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ግብሩን በታማኝነት በመክፈል ሃላፊነቱን እንዲወጣም አስገንዝበዋል።

በክልሉ የሚገኙ ከ115 ሺህ 790 በላይ የደረጃ የ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል ለክልሉ ልማት መጠናከር የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንዲያጠናክሩም ጠይቀዋል።

የገቢ አሰባሳብ ስርዓቱን በማዘመን ቀልጣፋና ፈጣን የገቢ አሰራርን ተግባራዊ መደረጉን ያነሱት ሃላፊዋ፣ ግብር ከፋዮችም የጊዜና ጉልበት ብክነትን በሚታደጉ የቴክኖሎጂ አማራጮች ተጠቅመው ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026