የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቡታጅራ፤ ሰኔ 30/2018 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ሃላፊ ቀመሪያ ረሻድ የቢሮውን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫን በማስመልከት ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

በክልሉ ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ በተሰራው ሥራ ውጤት መገኘቱንና ይህንንም አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በ2018 በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መቻሉንም አስታውቀዋል።

የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ9 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።

በቀጣይም የግብር አሰባሰብ ሥራውን ለማሳካት የግብር ህጉን የማስከበርና ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎች በተከታታይነት እንደሚሰሩ አንስተዋል።

በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሂደትንና ቅንጅታዊ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስረድተዋል።

በዚህም ክልሉ በ2019 በጀት ዓመት ከ33 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ለመሰብሰብ መታቀዱን ያነሱት ሃላፊዋ፣ ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ግብሩን በታማኝነት በመክፈል ሃላፊነቱን እንዲወጣም አስገንዝበዋል።

በክልሉ የሚገኙ ከ115 ሺህ 790 በላይ የደረጃ የ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል ለክልሉ ልማት መጠናከር የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንዲያጠናክሩም ጠይቀዋል።

የገቢ አሰባሳብ ስርዓቱን በማዘመን ቀልጣፋና ፈጣን የገቢ አሰራርን ተግባራዊ መደረጉን ያነሱት ሃላፊዋ፣ ግብር ከፋዮችም የጊዜና ጉልበት ብክነትን በሚታደጉ የቴክኖሎጂ አማራጮች ተጠቅመው ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 8, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 4, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026