🔇Unmute
ጅማ ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- ኢትዮጵያ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት የሄደችበት መንገድ ተጨባጭ ለውጥ እያሳየ መሆኑን ምሁራን ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ትላንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማስፋፋትና ለማዘመን ከተያዙ ቁልፍ ዘርፎች መካከል የኢንዱስትሪው ክፍለ-ኢኮኖሚ ዋነኛውና የትኩረት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰዋል።
ከለውጡ በፊት በሀገሪቱ የነበሩ ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ከ47 በመቶ በታች እንደነበር ጠቅሰው፤ ለዚህም እንደ ፋይናንስ፣ መሬትና የኃይል አቅርቦት ችግሮች በምክንያትነት ይጠቀሱ እንደነበር ገልጸዋል።
ይህንን ችግር ለመቅረፍ መንግሥት ልዩ ኮሚቴ በማቋቋም እያንዳንዱን ኢንዱስትሪ በመጎብኘትና ችግሮቻቸውን በየደረጃው ለመፍታት ባደረገው የተቀናጀ ጥረት፣ ቀድሞ የነበሩ ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅማቸው ዛሬ ላይ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል፡፡
እያደጉ የመጡት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪዎች በርካታ ምርቶችን በሰፊው በማምረት ከውጭ የሚገቡትን ምርቶች በሀገር ውስጥ ከመተካት ባለፈ፣ ወደ ውጭ የሚላከውን መጠን ከፍ አድርገውታል።
በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የዘርፉ ምሁራን እንደገለጹት፤ መንግስት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት የሄደበት መንገድ ተጨባጭ ለውጥ እያሳየ ነው።
በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር መስፍን መኮንን (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ባለፉት ዓመታት የውጭ ምንዛሬ እጥረት በትልቅ ተግዳሮትነት የቆየ ቢሆንም አሁን ላይ ግን ችግሩ በፍጥነት እየተቀረፈ ይገኛል።
አዳዲስ የኢንዱስትሪ ፓርኮች መገንባታቸውና የማምረት አቅማቸው በየጊዜው እንዲያድግ በተደረገው ጥረት በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል ብለዋል።
አክለውም ኢንዱስትሪዎች የሀገር ውስጥ ምርቶችን በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ በማቅረብ የውጭ ምርቶችን እያስቀሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ለዚህም የጨርቃ ጨርቅና የቆዳ ውጤቶችን ለአብነት በማንሳት በዚህ ሂደት እያደገ የመጣውን የሀገሪቱን የዲጂታል የቴክኖሎጂ አቅም አጋዠ እንደነበርም ገልጸዋል።
በተጨማሪም በምግብ ራስን ለመቻል ግብርናውን አዘምኖ በስፋት የማምረት ስራ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ መሆን የሚችል መሆኑን በመግለጽ፣ መንግስት በቀጣይ ይፋ ያደረጋቸውና እየሰራባቸው ያሉ ጉዳዮች ከዚህ የተሻለ ለውጥ እንደሚያመጡ ተናግረዋል።
ከውጭ የሚገቡ መድኃኒቶችን አስቀርቶ በሀገር ውስጥ የማምረት አቅም እያደገ መምጣቱ፣ እንዲሁም የማዳበሪያ ፋብሪካ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ከውጭ የሚገቡ የግብርና ግብዓቶችን ለማስቀረት የታቀደው ስራ ሀገሪቱን ወደፊት ተወዳዳሪ የሚያደርግ መሆንንም አስረድተዋል።
በጅማ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ምጣኔ ባለሙያ እና ተመራማሪ አደባ ገመቹ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ እንደ ስንዴ እና ሩዝ ያሉ ሰብሎችን በስፋት በማምረት ከውጭ የሚገባውን ምርት ለመቀነስና ለማስቀረት ስኬታማ ስራዎችን ማከናወኗን ገልጸዋል።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመሸፈን የሚደረገው ጥረት ለወጣቶችና ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የስራ እድል እና የገበያ ትስስር እየፈጠረ ይገኛል ብለዋል።
ቀደም ሲል በሀገር ውስጥ አይመረቱም ተብለው ይታሰቡ የነበሩ ምርቶች አሁን ላይ በጥራት እየተመረቱ መሆኑን በመጥቀስ ይህም የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎችንና ምርቶችን ማበረታታት በአቅርቦት ሰንሰለቱ ውስጥ ተጨማሪ የስራ እድሎችን ይፈጥራል ብለዋል።
ይህ ጥረት በምግብ ምርት ላይ ያለንን የውጭ ሀገራት ጥገኝነት በመቀነስ፣ ሀገራዊ የምግብ ዋስትናን በአስተማማኝ ሁኔታ ለማረጋገጥ የሚረዳ በመሆኑ ኢትዮጵያ ለዚህ ተጨባጭ ስኬት በትጋት እየሰራች መሆኗን ገልጸዋል፡፡
የፋብሪካዎች መስፋፋትም ለዚህ ግብ መሳካት መሠረት እየሆኑ መምጣታቸውን ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 8, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 4, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...
Jun 17, 2026