🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል በ2018 በጀት አመት ከ4 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ያሲን አብዱላሂ ገልጸዋል።
ኃላፊው እንደተናገሩት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚታቀዱ ፕሮጀክቶች እውን እንዲሆኑ በተለይም ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ወሳኝ ነው።
በመሆኑም በተጠናቀቀው በጀት አመት የክልሉን ገቢ አሟጦ ከመሰብሰብ አንፃር ዘርፈ ብዙ ርብርብ ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰዋል።
በዚህም በአመቱ 4 ቢሊየን 672 ሚሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ4 ቢሊየን 625 ሚሊየን ብር በላይ በመሰብሰብ፣ የእቅዱን 99 በመቶ ማሳካት መቻሉን ጠቁመዋል።
ከተሰበሰበው ገቢ መካከልም በቀጥታ ታክስ ከ2 ቢሊየን 612 ሚሊየን ብር በላይ፣ ቀጥታ ካልሆነ ታክስ 2 ቢሊየን 211 ሚሊየን ብር፣ ታክስ ነክ ካልሆነ ገቢ ደግሞ ከ275 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን ጠቁመዋል።
እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ደግሞ ከ526 ሚሊየን ብር በላይ የተሰበሰበ መሆኑን ተናግረዋል።
ገቢው ከ2017 ተመሳሳይ ዓመት ጋር ሲነፃፀርም ከ1 ቢሊየን 516 ሚሊዮን በላይ ብልጫ እንዳለውም ነው የገለጹት።
በተለይም የውስጥ መናበብን በማሳደግና ቅንጅታዊ አሰራርን በማጎልበት፤ አገልግሎት አሰጣጥን በማሳደግ፤ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራርን መዘርጋቱ፤ ውዝፍ እዳን አሟጦ መሰብሰቡ እና የቅሬታ አፈታት ስርዓትን ማሻሻል ለገቢ አሰባሰቡ መሻሻል እገዛ አንዳደረገ አስረድተዋል።
የታክስ ተደራሽነት ማስፋትና ብቃትና ተጠያቂነትን መሠረት ያደረገ የሰው ኃይል ስምሪትና አመራር መተግበር መቻሉም ሌላው ለገቢው ማደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ጉዳይ መሆኑን ጠቁመዋል።
የአሰራር ስርዓት ላይ የነበሩ መመሪያዎችን በማሻሻል እና ህገ-ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊነት የመቀየር ስራ በትኩረት መሰራቱ በዓመቱ የታቀደው እቅድ እንዲሳካ አስችሏል ብለዋል።
በ2019 የበጀት በጀት ዓመትም ከግብር ከፋዩና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ እና ለተጀመረው ክልላዊና ሀገራዊ የብልፅግና ጉዞ በብቃት ኃላፊነትን ለመወጣት ዝግጅት እየተደረገ ስለመሆኑም አንስተዋል።
በዓመቱ የተከናወነው የገቢ አሰባሰብ እንዲጎለብት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በተለይም ለታማኝ ግብር ከፋዮች፣ የተቋሙ ሰራተኞች፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የቢሮው ኃላፊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 8, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 4, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...
Jun 17, 2026