🔇Unmute
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 4/2018 (ኢዜአ):- በሀገሪቱ በወጪ ንግድ የተመዘገበውን ውጤት ይበልጥ ለማሳደግ በምርት ጥራትና እሴት መጨመር ላይ በትኩረት እንደሚሰራ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክን የሥራ እንቅስቃሴ የጎበኙ ሲሆን፣ በፓርኩ የአቮካዶ፣ ዘይትና ቡናን የሚያቀናብሩ ኩባንያዎችን ተመልክተዋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ መንግሥት የወጪ ንግድ ገቢን ለማሳደግ በእሴት መጨመር ሥራ ላይ የሚደረጉ ጥረቶችን ለማጠናከር ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል።
በተለይም በግብርናው ዘርፍ ያለውን አቅም በአግባቡ በመጠቀምና ገበያው በሚፈልገው መልኩ እሴት ጨምሮ መላክ ላይ የተጀመሩ ጥረቶች የሚጠናከሩ ናቸው ብለዋል።

በፓርኩም በአቮካዶና በቡና ዘርፍ በመሰማራት እሴት በመጨመር የወጪ ገቢ ግኝትና ተኪ ምርት ላይ የተሰማሩ ኩባንያዎችን መመልከታቸውን ጠቅሰው፤ ተግባሩን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በዘንድሮ ዓመት ከወጪ ንግድ ከ11 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ በማግኘት ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ መቻሏን ያወሱት ሚኒስትሩ፤ በፓርኩ የሚታዩ እንቅስቃሴዎችን ማሳደግ ይገባልም ብለዋል።
በእስካሁኑ ሂደትም ተኪ ምርቶች ላይ እንደሀገር እየተገኘ ያለውን ውጤት ለማጠናከር የሚደረጉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
በዚህ ሂደት ደግሞ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች መቋቋማቸው ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል።

በኢንዱስትሪ ፓርኩ ቡናን በማቀነባበር ስራ ላይ የተሰማራው የ“መይ መይ ቡና ፕሮሰሲንግ” ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ጄይ ሰን፣ በመንግሥት በተደረገላቸው ድጋፍ ታግዘው ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 8, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 4, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...
Jun 17, 2026