የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል የሕዝብን መሠረታዊ ጥያቄዎች መፍታት ያስቻሉ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል

Jul 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሐምሌ 6/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ዓመታት የሕዝብን መሠረታዊ ጥያቄዎች መፍታት ያስቻሉ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።

የኦሮሚያ ክልል የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመንግሥትና የፓርቲ ሥራ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በአዳማ ከተማ አባ ገዳ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።


በዚሁ ወቅት የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በክልሉ ሕዝብ ሲነሱ የነበሩ የልማት ጥያቄዎች በተጨባጭ ምላሽ አግኝተዋል ብለዋል።

በተለይም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፎች ስኬታማ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸው፤ በዚህ ሂደት አመራሩ የክልሉን ሰላም በማረጋገጥ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማቶች እንዲሳለጡ አድርጓል ነው ያሉት።

የመንግሥትን በጀት እና የሕዝብ ተሳትፎን በማቀናጀት የሕዝቡን የመልማት ጥያቄ ለመመለስ የተደረገው ርብርብ ውጤታማ እንደነበርም አንስተዋል።

ይህም በመሆኑ የክልሉ አመራር የተገኙ ድሎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችሉ ስልቶችን መፈተሽና የታዩ ክፍተቶችን በመለየት ቀጣይ ሥራዎች መዘጋጀት አለባቸው ብለዋል።

በቀጣዩ በጀት ዓመትም በክልሉ ካለው እምቅ አቅምና የልማት ፍላጎት ጋር የሚጣጣም የተለጠጠ ዕቅድ በማዘጋጀት፣ ያሉትን አማራጮች አሟጦ መጠቀም እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።


በተለይም የቤተሰብ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በቁጠባ ላይ በትኩረት መሥራት የሚገባ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳለጥ በዞኖች፣ በወረዳዎችና በከተሞች ያሉ ምቹ ሁኔታዎችን መፈተሽና ሥራ ላይ ማዋል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ክልል ያለው የአመራርነት አቅምና ብቃት በግምገማው በመፈተሽ በተገኙ ውስን ድሎች ሳይዘናጉ አሁንም በሙሉ አቅም መረባረብ ይገባልም ብለዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ በበኩላቸው፣ በበጀት ዓመቱ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሪፎርሞችን ወደ ተግባር በመቀየር ረገድ ተስፋ ሰጪ ድሎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።


በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ብቻ 21 ሺህ የሚጠጉ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለሕዝብ አገልግሎት እንዲበቁ መደረጉን አንስተው፤ ይህም የዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም ውጤታማ ቢያደርገውም፣ አፈጻጸሙ በሁሉም ዞኖችና ከተሞች ወጥነት ያለው አለመሆኑን ጠቅሰዋል።

በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ በነቂስ በመውጣት ለዴሞክራሲ ያለውን ፅኑ ፍላጎት ያሳየበትና ትልቅ የፖለቲካ ድል የተመዘገበበት መሆኑን የጠቀሱት አመራሮቹ፤ በተያዘው አዲሱ የበጀት ዓመት አመራሩ በሙሉ አቅሙና ቁርጠኝነት መረባረብ እንደሚገባው አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026