የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ለማሳደግ የተተገበሩ አሰራሮች ውጤት አስገኝተዋል

Jul 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሐምሌ 6/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ በግብርና ዘርፍ የተተገበሩ አሰራሮች ውጤት ማስገኘታቸውን የክልሉ ፕላንና ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር አብዲ ያዩ (ዶ/ር) ገለፁ።

የክልሉ የመንግሥትና የፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዘርፍ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄደ ይገኛል።


በግምገማው መድረክ ላይ ዝርዝር ሪፖርት ያቀረቡት የክልሉ ፕላንና ልማት ኮሚሽነር አብዲ ያዩ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት ለማሳደግ የተተገበሩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችና የተደረጉ ሁለንተናዊ ድጋፎች ከፍተኛ ውጤት አስገኝተዋል።

ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በከተሞችና በገጠር አካባቢዎች የወተት ላሞች እርባታ በዘመናዊ መንገድ መተግበሩና ምርጥ የእርባታ ዶሮዎች ለአርሶ አደሩ መሰራጨታቸው መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም በዓሣ እርባታ ዘርፍ ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ የዓሣ ጫጩቶች ለአርሶ አደሩና ለአርብቶ አደሩ ተሰራጭተው ወደ እርባታ ኩሬዎች መግባታቸውን ገልጸዋል።

የአርሶ አደሩን የሰብል ልማት ውጤታማነት በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና በቅርበት የገበያ ትስስር የሚያገኝበት ምቹ የገበያ ማዕከላት መገንባታቸውን ኮሚሽነሩ ጠቅሰዋል።

ይህም የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደጉ ባለፈ፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም ትልቅ እገዛ ማድረጉን አስረድተዋል።

በክልሉ የሚታየውን የሥራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ በተደረገው ሰፊ ጥረትም በበጀት ዓመቱ ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አዲስ የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል ብለዋል።

የክልሉን ሁለንተናዊ ልማት በራስ አቅም ለመሸፈን በተደረገው የውስጥ ገቢ ማሰባሰብ ጥረትም የተሻለ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ገልጸዋል።


በበጀት ዓመቱ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት በተደረገው የተቀናጀ ጥረት 13 ሺህ 147 አዳዲስ አልሚ ባለሀብቶችን መሳብ ተችሏል ነው ያሉት።

ይህንን ተግባር ይበልጥ ለማስቀጠልም አርሶ አደሮችና የአገር ውስጥ አንቀሳቃሾችን በመደገፍ፣ ሀብት አፍርተው ከእርሻ ሥራ ወደ ኢንቨስትመንት ባለቤትነት እንዲሻገሩ መደረጉን ጠቅሰዋል።

የሕዝቡን የማኅበራዊ አገልግሎት ተደራሽነት ለማረጋገጥ በተደረገው ጥረትም በትምህርት፣ በጤና፣ በንጹህ መጠጥ ውኃና በመንገድ ልማት ዘርፎች እጅግ የተሻለና አበረታች አፈጻጸም መመዝገቡን አንስተዋል።

በአዳማ ከተማ አባ ገዳ አዳራሽ እየተካሄደ ያለው ይህ የመንግሥትና የፓርቲ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በቀጣዮቹ ቀናትም እንደሚቀጥል ከወጣው መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 8, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 4, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026