የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በምስራቅ ቦረና ዞን የገቢ አሰባሰብን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል

Jul 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነገሌ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን የገቢ አሰባሰብ ሒደቱን ዲጂታላይዝድ በማድረግ በበጀት ዓመቱ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የዞኑ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡

በጽሕፈት ቤቱ የዕቅድ፣ በጀት ክትትልና ግምገማ ባለሙያ መዓዛ አሊ እንዳሉት በዞኑ የገቢ አሰባሰብ ሒደት ቀልጣፋና ፍትሐዊ ለማድረግ የዲጂታል አሠራር ተዘርግቷል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ከተለያዩ የገቢ ርዕሶች ለመሰብሰብ ከታቀደው ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ውስጥ ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ገልጸዋል፡፡

ከዞኑ የተሰበሰበው ዓመታዊ ገቢ ከዕቅዱ በ311 ሚሊዮን 917 ሺህ ብር ብልጫ እንዳለው አስታውቀዋል፡፡

የገቢ አሰባሰቡን ውጤታማ ለማድረግም የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሠራር መዘርጋቱና ግብር መክፈል የዜግነት ግዴታ መሆኑን ተከታታይ የግንዛቤ መድረክ መፈጠሩን አንስተዋል።

ግብራቸውን በታማኝነትና በወቅቱ በመክፈል የዜግነት ድርሻቸውን መወጣታቸውን ያስረዱት ደግሞ በነገሌ ቦረና ከተማ የሕንጻ መሣሪያ አቅራቢና አከፋፋይ አቶ ወርቁ ኦዳ ናቸው።

የሚከፍሉት የሥራ ግብር ለመሠረተ ልማት ግንባታ በመዋል ተመልሶ ሕዝብን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን በመገንዘባቸው ግብርን በጊዜ መክፈላቸውን አክለዋል።


በከተማው በሸቀጣሸቀጥ ንግድ ሥራ የተሰማሩት አቶ ቢኒያም አሰፋ በበኩላቸው ግብርን መክፈል የዜግነት ግዴታ እና ለአገር ልማት ነው ብለዋል፡፡

በታማኝነት ግብር መክፈል ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣም አስተያየታቸውን አጋርተዋል።


የሚከፍሉት ግብር ለአገር ልማት የራሱ ድርሻ እንዳለው የጠቆሙት ደግሞ በንግድ ሥራ የተሰማሩት አቶ ሰይድ በድሩ ፤በታማኝነት ግብራቸውን በመክፈል ፍትሐዊ የንግድ ውድድር እንዲሰፍንና የሕዝቡ የመሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ የበኩላቸውን መወጣታቸውን ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 8, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 4, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026