🔇Unmute
ነገሌ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን የገቢ አሰባሰብ ሒደቱን ዲጂታላይዝድ በማድረግ በበጀት ዓመቱ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የዞኑ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡
በጽሕፈት ቤቱ የዕቅድ፣ በጀት ክትትልና ግምገማ ባለሙያ መዓዛ አሊ እንዳሉት በዞኑ የገቢ አሰባሰብ ሒደት ቀልጣፋና ፍትሐዊ ለማድረግ የዲጂታል አሠራር ተዘርግቷል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ ከተለያዩ የገቢ ርዕሶች ለመሰብሰብ ከታቀደው ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ውስጥ ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ከዞኑ የተሰበሰበው ዓመታዊ ገቢ ከዕቅዱ በ311 ሚሊዮን 917 ሺህ ብር ብልጫ እንዳለው አስታውቀዋል፡፡
የገቢ አሰባሰቡን ውጤታማ ለማድረግም የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሠራር መዘርጋቱና ግብር መክፈል የዜግነት ግዴታ መሆኑን ተከታታይ የግንዛቤ መድረክ መፈጠሩን አንስተዋል።
ግብራቸውን በታማኝነትና በወቅቱ በመክፈል የዜግነት ድርሻቸውን መወጣታቸውን ያስረዱት ደግሞ በነገሌ ቦረና ከተማ የሕንጻ መሣሪያ አቅራቢና አከፋፋይ አቶ ወርቁ ኦዳ ናቸው።
የሚከፍሉት የሥራ ግብር ለመሠረተ ልማት ግንባታ በመዋል ተመልሶ ሕዝብን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን በመገንዘባቸው ግብርን በጊዜ መክፈላቸውን አክለዋል።

በከተማው በሸቀጣሸቀጥ ንግድ ሥራ የተሰማሩት አቶ ቢኒያም አሰፋ በበኩላቸው ግብርን መክፈል የዜግነት ግዴታ እና ለአገር ልማት ነው ብለዋል፡፡
በታማኝነት ግብር መክፈል ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣም አስተያየታቸውን አጋርተዋል።

የሚከፍሉት ግብር ለአገር ልማት የራሱ ድርሻ እንዳለው የጠቆሙት ደግሞ በንግድ ሥራ የተሰማሩት አቶ ሰይድ በድሩ ፤በታማኝነት ግብራቸውን በመክፈል ፍትሐዊ የንግድ ውድድር እንዲሰፍንና የሕዝቡ የመሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ የበኩላቸውን መወጣታቸውን ጠቁመዋል፡፡
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026