🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2018(ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል በ2018 በጀት ዓመት በገጠርና ከተማ ከ72 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ መሠረተ ልማት መገንባቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩ ይህንን የገለፁት እየተካሄደ በሚገኘው የሐረሪ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ጉባዔው ላይ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት ነው።

በሪፖርታቸውም በክልሉ በመንገድ መሰረተ ልማት ደህንነትን፤ ፍትሃዊነትንና ተደራሽነትን ለማረጋገጥና የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎትን ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በተለይም በከተማና በገጠር አዳዲስ የመንገድ መሰረተ ልማት የመገንባትና ነባር የመንገድ መሰረተ ልማት የመጠገን ስራ ሲከናወን ቆይቷል ብለዋል።
የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ገጠርን ከከተማ እንዲሁም የገጠር ወረዳዎችን የሚያገናኙ መሆናቸውን ጠቁመው በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ በገጠርና ከተማ ከ72 ኪሎ ሜትር በላይ የአስፋልትና የጠጠር መንገዶች መገንባታቸውን ነው የተናገሩት።
በተጨማሪም በከተማ ከ8 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር በላይ በተለያዩ አካባቢዎች የመንገድ ድሬኔጅ የመገንባትና የመጠገን ስራዎች በትኩረት መከናወናቸውን ርዕሰ መስተደድሩ ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 8, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 4, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...
Jun 17, 2026