የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ በበጀት ዓመቱ በገጠርና ከተማ ከ72 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ መሠረተ ልማት ተገንብቷል 

Jul 18, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 9/2018(ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል በ2018 በጀት ዓመት በገጠርና ከተማ ከ72 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ መሠረተ ልማት መገንባቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ ይህንን የገለፁት እየተካሄደ በሚገኘው የሐረሪ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ጉባዔው ላይ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት ነው።


በሪፖርታቸውም በክልሉ በመንገድ መሰረተ ልማት ደህንነትን፤ ፍትሃዊነትንና ተደራሽነትን ለማረጋገጥና የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎትን ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በተለይም በከተማና በገጠር አዳዲስ የመንገድ መሰረተ ልማት የመገንባትና ነባር የመንገድ መሰረተ ልማት የመጠገን ስራ ሲከናወን ቆይቷል ብለዋል።

የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ገጠርን ከከተማ እንዲሁም የገጠር ወረዳዎችን የሚያገናኙ መሆናቸውን ጠቁመው በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ በገጠርና ከተማ ከ72 ኪሎ ሜትር በላይ የአስፋልትና የጠጠር መንገዶች መገንባታቸውን ነው የተናገሩት።

በተጨማሪም በከተማ ከ8 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር በላይ በተለያዩ አካባቢዎች የመንገድ ድሬኔጅ የመገንባትና የመጠገን ስራዎች በትኩረት መከናወናቸውን ርዕሰ መስተደድሩ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 8, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 4, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026