የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ35 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል

Jul 18, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቡታጅራ ፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት ከ35 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ገለጸ።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የገቢ ዕቅድ ተግባቦት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በቡታጅራ ከተማ ተካሂዷል።


የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ቀመሪያ ረሻድ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ገቢን አሟጦ የመሰብሰብ ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በ2019 በጀት ዓመት የክልሉን ገቢ የማመንጨት አቅምንና የማኅበረሰቡን የልማት ጥያቄ ታሳቢ በማድረግ ከ35 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ የሚያስችል የገቢ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ተግባር ስለመገባቱም ተናግረዋል።

የድጋፍና ክትትል ሥራን በማጠናከር፣ አገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ቀልጣፋ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ዕቅዱን ለማሳካት ይሠራል ነው ያሉት፡፡

ከተሳታፊዎች መካከል የስልጤ ዞን የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ከድር አደም በሰጡት አስተያየት፤ ግብር ለአካባቢው ማኅበረሰብ የልማት ጥያቄ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ያለው ሚና ከፍተኛ ነው።


በዞኑ በ2018 በጀት ዓመት የተገኘውን ልምድ በመቀመር በ2019 በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱንም አመልክተዋል።

በልዩ ወረዳው ያለውን የገቢ አማራጭ አሟጦ በመሰብሰብ ወጪን በራስ ገቢ ለመሸፈን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ እንዳሻው አበራ ናቸው።

በልዩ ወረዳው እየተመዘገበ ያለውን ዕድገት ለማስቀጠልም በ2019 በጀት ዓመት ከ505 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 8, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 4, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026