🔇Unmute
ቡታጅራ ፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት ከ35 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ገለጸ።
የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የገቢ ዕቅድ ተግባቦት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በቡታጅራ ከተማ ተካሂዷል።

የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ቀመሪያ ረሻድ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ገቢን አሟጦ የመሰብሰብ ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በ2019 በጀት ዓመት የክልሉን ገቢ የማመንጨት አቅምንና የማኅበረሰቡን የልማት ጥያቄ ታሳቢ በማድረግ ከ35 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ የሚያስችል የገቢ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ተግባር ስለመገባቱም ተናግረዋል።
የድጋፍና ክትትል ሥራን በማጠናከር፣ አገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ቀልጣፋ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ዕቅዱን ለማሳካት ይሠራል ነው ያሉት፡፡
ከተሳታፊዎች መካከል የስልጤ ዞን የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ከድር አደም በሰጡት አስተያየት፤ ግብር ለአካባቢው ማኅበረሰብ የልማት ጥያቄ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ያለው ሚና ከፍተኛ ነው።

በዞኑ በ2018 በጀት ዓመት የተገኘውን ልምድ በመቀመር በ2019 በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱንም አመልክተዋል።
በልዩ ወረዳው ያለውን የገቢ አማራጭ አሟጦ በመሰብሰብ ወጪን በራስ ገቢ ለመሸፈን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ እንዳሻው አበራ ናቸው።
በልዩ ወረዳው እየተመዘገበ ያለውን ዕድገት ለማስቀጠልም በ2019 በጀት ዓመት ከ505 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቅሰዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026