የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቻይና-አፍሪካ ትብብርን ይደግፋል - አንቶኒዮ ጉቴሬዝ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 30 /2016(ኢዜአ)፡- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቻይናና አፍሪካ ትብብርና አጋርነትን እንደሚደግፍ የድርጅቱ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ።

የቻይና-አፍሪካ ጉባኤ ዛሬ በቤጂንግ መካሄድ ጀምሯል።

የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ላይ ዓለም በግጭቶችና ማህበራዊ ቀውሶች ውስጥ እያለፈች እንደምትገኝና ተግዳሮቶቹ ለእድገትና ልማት ትልቅ ፈተና መሆናቸውን ገልጸዋል።

የአፍሪካ አገራት በእዳ ቀውስ ፈተና ውስጥ መግባታቸውንና ለዘላቂ ልማት መዋዕለ ንዋይ ለማፍሰስ መቸገራቸውን አመልክተዋል።

ኢ-ፍትሐዊና ጊዜው ያለፈበት ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ማሻሻያ እንደሚያስፈልገውና የፋይናንስ ተቋማት ፍትሐዊ በሆነ መልኩ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

በማደግ ላይ የሚገኙ አገራት ፈታኝ የገበያ ሁኔታዎች ተቋቁመው የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ የሚያደርግ የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፍ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ይህም የአገራትን የፋይናንስ ተደራሽነት በማሳደግ የመካከለኛና የረጅም ዘመን መፍትሔ እንዲያበጁ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓቱ ፍትሐዊ ማሻሻያ ለማድረግ የአፍሪካና ቻይና ሚና ቁልፍ መሆኑን ነው ዋና ፀሐፊው የገለጹት።

ከዚህ አኳያም የደቡብ-ደቡብ ትብብር የአገራትን አቅም ለመገንባትና የልማት ግቦችን በጋራ እውን ለማድረግ የሚያስችል ማዕቀፍ እንደሆነ ተናግረዋል።

ቻይና ከአፍሪካ ጋር ያላት አጋርነት የደቡብ-ደቡብ ትብብር ዋንኛ ምሰሶ ነው ብለዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቻይና-አፍሪካ ትብብርና አጋርነት እንደሚደግፍ ዋና ፀሐፊው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026