
አዲስ አበባ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ ባለፉት ስድስት ወራት ከ112 ሺህ በላይ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እየተከታተሉ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ 5 ሚሊዮን ዜጎችን የዲጅታል ክህሎት እንዲያገኙ የሚያስችል የኮደርስ ኢኒሼቲቭ እየተተገበረ ይገኛል።
አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚሰጠው ስልጠናም የዳታ ሳይንስ፣ ኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ ሞባይል አንድሮይድና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፎችን ያካትታል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሰለሞን አማረ ለኢዜአ እንዳሉት የኮደርስ ስልጠና በአዲስ አበባ የስማርት ሲቲ ፕሮጀክትን እውን ለማድረግ ትልቅ አቅም ይፈጥራል።
በተለይም የዲጂታል እውቀትና ክህሎታቸው ያደገ ሙያተኞችን ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በ2017 በጀት ዓመት እስክ ታህሳስ 30 ድረስ ከ112 ሺህ በላይ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እየተከታተሉ እንደሚገኙም ገልጸዋል።
ከእነዚህ መካከልም እስከ 30 ሺህ የሚሆኑ ወጣቶች ስልጠናውን በሚገባ በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ተናግረዋል።
በከተማ አስተዳደሩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በቴክኖሎጂ ሥርዓት እንዲተሳሰሩ መደረጋቸውን ጠቅሰው፥ የኮደርስ ስልጠናው አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ ያስችላል ነው ያሉት።
ከአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሙያተኞች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መሰጠት መጀመሩንም ገልጸዋል።
ሁሉም ቢሮዎች የኮደርስ ኢኒሼቲቭን የሚከታተል ቡድን አቋቁመው እንዲሠሩ እየተደረገ መሆኑንም ጨምረው አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026