የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር 23/2017(ኢዜአ)፦ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የወሰዱ ዜጎች ቁጥር 11 ነጥብ 5 ሚሊዮን መድረሱን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል፡፡

የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ የነዋሪዎችን የባዮሜትሪክ (የጣት አሻራ፣ የአይን አይሪስ እና የፊት ምስል) እንዲሁም የግል መረጃዎችን በመሰብሰብ አንድን ግለሰብ ልዩ በሆነ መልኩ እንዲታወቅ የሚያስችል ነው፡፡

ይህም ዘመናዊ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓትን በመገንባት ማንነትን የማረጋገጥ ሂደት ቀልጣፋ እና ደህንነቱ የተረጋገጠ እንዲሆን ያደርጋል።

የፕሮግራሙ የስትራቴጂክ የኮሙኒኬሽን አማካሪ አቶ አቤኔዘር ፈለቀ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ፕሮግራሙ ከተጀመረ አመታት ማስቆጠሩን ተናግረዋል።

በነዚህ አመታት ውስን በፕሮግራሙ የታቀዱ ውጥኖች ማሳካት የሚያስችሉ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል።


እስከ አሁን ድረስ ከ1 ሺህ በላይ በሆኑ የምዝገባ ጣቢያዎች 11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች መታወቂያውን መውሰዳቸውን አስታውቀዋል።

ከ52 ተቋማት ጋር ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ትግበራና የአሰራር ትስስር መዘርጋት የሚያስችል ስራ መሰራቱንም ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅትም ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን 12 የሚደርሱ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንደ ቅድመ ሁኔታ በማስቀመጥ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙም ገልጸዋል።

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የሕግና ፖሊሲ ክፍል ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም በበኩላቸው፥ በ2017 ዓ.ም የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባ በተጠናከረ አግባብ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

በዚህም በተቋሙና በምዝገባ ሂደት አጋር በሆነው ኢትዮ ቴሌኮም አማካኝነት በአገር አቀፍ ደረጃ ምዝገባ እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል።


ይህም በከተሞች ብቻ የነበረውን ምዝገባ በገጠር አካባቢዎችም ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰው፥ ይህም በዓመቱ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።

ምዝገባውን በድንበር አካባቢዎችም ተደራሽ ለማድረግ በግል ተቋማት የሚከናወን ሱፐርኤጀንት የሚባል አሰራር ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተግባራዊ መደረጉ ሁሉን አቀፍ፣አካታችና አስተማማኝ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችልም ተመላክቷል።

ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ዘርፈ ብዙ አስፈላጊነትን በመገንዘብ በአቅራቢያቸው በሚገኙ የመመዝገቢያ ጣቢያዎች በመመዝገብ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ እንዲሆኑም ኃላፊዎቹ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026