የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>የአካባቢያችንን ሰላም ለማፅናትና ልማትን ለማፋጠን ድጋፋችንን እናጠናክራለን - በአርጡማ ፉርሲ ወረዳ ነዋሪዎች</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፡- የአካባቢያቸውን ሰላም ለማፅናትና ልማትን ለማፋጠን ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አርጡማ ፉርሲ ወረዳ አስያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ነዋሪዎች ገለጹ።

በህብረተሰቡ ተሳትፎ ሰላምን በማስከበር የልማት ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የወረዳው አስተዳደር አመልክቷል።

በወረዳው የወገሬ ደቢሳ ቀበሌ ነዋሪ አቶ አህመድ አወል ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ ሰላማቸውን በመጠበቅ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

ሰላምን በማፅናት የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ የአካባቢው አስተዳደር እያደረገ ያለውን ጥረት እንደሚደግፉም ተናግረዋል።


ሌላዋ የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ከድጃ የሱፍ፤ የአካባቢያችን ሰላም በመጠበቁ አሁን ላይ በተለያዩ ተፋሰሶች የአፈርና ውሃ እቀባ ስራ እያከናወንን እንገኛለን ብለዋል፡፡

የአካባቢያቸውን ሰላም በማፅናት ልማትን ለማፋጠን ድጋፋቸውን በቁርጠኝነት እንደሚያጠናክሩ አስተያየት ሰጪዎቹ ገልጸዋል።


ህብረተሰቡን በማሳተፍ የአካባቢውን ሰላም ማስጠበቅ መቻሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ በትኩረት እንዲሰራ አስችሏል ያሉት ደግሞ የብሔረሰብ አስተዳደር ዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ ናቸው።

ለዚህም ከአጎራባች አካባቢዎች ጋር በመቀናጀት ሰላም ማስጠብቅ የሚያስችል ውይይትና ምክክር በየጊዜው መካሄዱን ጠቅሰዋል።

ይህም የአካባቢው ሰላም እንዲጠበቅ ምቹ መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል።

በመሰረት ልማት፣ በመስኖ፣ በሥራ እድል ፈጠራ፣ በበጋ በጎ ፈቃድና በሌማት ትሩፋት ላይ በማተኮር አበረታች ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉንም አብራርተዋል።

የተገኘውን ውጤት ዘላቂ ለማድረግም ህብረተሰቡ አንድነቱን ጠብቆ ሰላሙን ለማጽናት በቁርጠኝነት መስራቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ በአርጡማ ፉርሲ ወረዳ እየተከናወነ መሆኑን ቀደም ሲል መዘገባችን ይታወሳል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026