የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ከዓለም ፈጣን የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር የሚያወዳድር ነው

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ በሳይንስ ሙዚየም የተከፈተው ቋሚ ኤግዚቢሽን ኢትዮጵያን ከዓለም ፈጣን የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር የሚያወዳድርና የትውልዱን መጻዒ ዕድል በፈጠራና ምርምር የሚያግዝ መሆኑን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽንን በይፋ ከፍተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገን መስራት፣ ማየት እና መለማመድ የሚፈልጉ ሰዎች በሙሉ የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽንን እየመጡ መመልከት አለባቸው ብለዋል።

ኢትዮጵያውያን ነገን መስራት ነገን መለወጥ ከፈለጉ ልጆቻቸውን ወደ ኤግዚቢሽኑ ሊያመጧቸው እንደሚገባም አመልክተዋል።

ልጆቻችንም ይህ ትልቅ ዕድል እንደሆነ ተገንዝበው ክረምቱን ይህንን ቋሚ ኤግዚቢሽን በማየት ብዙ ትምህርት መቅሰም አለባቸው ሲሉም ገልጸዋል።

ኤግዚቢሽኑ በውስጡ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የአካባቢ፣ የግብርና፣ የውሃና ኢነርጂ፣ የስፔስና አቪየሽን ማሳያ ክፍሎችን አካቷል።

በዕለቱ ቋሚ ኤግዚቢሽኑን የቱሪዝም፣ የኪነ ጥበብ፣ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና ታዋቂ ግለሰቦች ጎብኝተውታል።

አስተያየታቸውን የሰጡ ጎብኚዎችም ኢትዮጵያ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ባከናወነቻቸው ሥራዎች መደመማቸውን ነው ያነሱት።

የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ነጋ ወዳጆ ቴክኖሎጂን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ምን ያህል ውጤታማ ሊያደርግ እንደሚችል ያየንበት ነው ብለዋል።

ሰው ሰራሽ አስተውሎት በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርትና በሌሎች ዘርፎች አጋዥ በመሆኑ ትውልዱ ሳይንስን በአግባቡ በመረዳት ለአዳዲስ ፈጠራዎች እንዲተጋ የሚያግዝ መሆኑንም አመልክተዋል።


የፍሎውረስ ኢቨንትስ ስራ አስኪያጅ ዮአዳን ጥላሁን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የቋሚ ኤግዚቢሽኑ መከፈት ተማሪዎች ሳይንስ ላይ የተመሰረተ ተጨባጭ ፊልምና ትርኢት የማየት ዕድል እንዲያገኙና ከቴክኖሎጂ ጋር በደንብ እንዲተዋወቁ ያስችላል።

በቋሚ ኤግዚቢሽኑ ኢትዮጵያን በዓለም ተወዳዳሪ የሚያደርጉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን አይቻለሁ የሚሉት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ረዳት መምህር ማስተር ምህረት ከድር ናቸው።


ጋዜጠኛ አስካለ ተስፋዬ በበኩሏ፤ በሳይንስ ሙዚየም በቴክኖሎጂ የታገዘ የፈጠራ ትርኢትና ፊልም በአድናቆት መመልከቷን ገልጻለች።

ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ትልቋ ኢትዮጵያን ከማሳየት ባለፈ የተፈጥሮ ጸጋ፣ የእድገትና የቴክኖሎጂ ልህቀት መሻቷን የሚያሳይ እንዲሁም ለተማሪዎች የነገ ተስፋ ለተመራማሪዎች ደግሞ ምቹና ሁሉን ያቀፈ ማዕከል መሆኑን ነው ያብራራችው።


ጋዜጠኛ ዮናስ ከበደ በሙዚየሙ የትናንት፣ የዛሬና የነገ ማንነታችንን ያየንበት ነው ብሏል።

ኢትዮጵያ አሁን ላይ የደረሰችበት ከፍታ ትናንትን ያልረሳና ትውልድን ያስተሳሰረ መሆኑ ሁሉንም የሚያኮራ መሆኑን በማንሳት።


ጋዜጠኛ ዳዊት አበበም የሰው ሰራሽ አስተውሎት የሰው ልጆችን ህይወት በማቅለል በኩል የደረሰበትን ደረጃ በቀላሉ ማየትና በዚያ መጠቀም የሚያስችሉ ዕድሎች መፈጠራቸውን አድንቋል።


የሳይንስ ሙዚየምን በሰለጠኑ ሀገራት የመመልከት ዕድል እንደነበረውና በአጭር ጊዜ በኢትዮጵያ እውን ሆኖ ማየቱ አግራሞት እንደፈጠረበት የገለጸው ደግሞ አርቲስት ዳንኤል ተገኝ ነው።

በሙዚየሙ ያገኘውን ዕድል ተጠቅሞ ለሀገርና ህዝብ ጠቃሚ የሆነ ፊልም ለመስራት ፍላጎት አንዳደረበት ጠቅሷል።


በቋሚ ኤግዚቢሽኑ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የህዋ ቅርጽ ሉላዊ የትዕይንት አዳራሽ ይፋ የተደረገ ሲሆን ስለ-ህዋ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው እጅግ አስደማሚ ምስሎችን በማቅረብ የህዋውን አለም እጅግ አቅርቦ ያሳያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026