🔇Unmute
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።
ጳጉሜን 5 የነገው ቀን በአማራ ክልል በተለያዩ መርሃ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ፤ የነገውን የሀገርን ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ብለዋል።
የዛሬው ትጋታችን ለነገ ከተስፋም ባለፈ ፍሬ የሚያፈራ በመሆኑ በሁሉም ረገድ የጀመርናቸው የልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አፅኖት ሰጥተዋል።
የክልሉ መንግሥት የነገውን ትውልድና የሀገር ተስፋ በማሰብ የአሻጋሪ ዕድገት እና የዘላቂ ልማት አቅዶችን ለማሳከት የተቀናጀ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የነገ ዋስትናችን ዛሬ በመሆኑ የቀጣዩን ትውልድ ተስፋ ለማሳመር በቴክኖሎጂና ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ላይ በማተኮር መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።
ርእሰ መስተዳድሩ በማጠቃለያ መልእክታቸው አዲሱ ዓመት ለክልሉ ህዝብና ለመላው ኢትዮጵያዊያን የሰላም፣ የፍቅርና የስኬት እንዲሆን ተመኝተዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026