የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ባለፉት ስድስት ዓመታት የተከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ተግባራት ውጤት እያመጡ ነው

Jul 14, 2025

IDOPRESS

ጉራፈርዳ፣ ሐምሌ 5/2017 (ኢዜአ)፡-ባለፉት ስድስት ዓመታት የተከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ተግባራት ውጤት እያመጡ መሆናቸውን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና ሴክተር ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አክሊሉ ታደሰ ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትና በተጠሪ ተቋማት በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በ35 ሚሊዮን ብር ወጪ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ለሚገነቡ መኖሪያ ቤቶችና ሞዴል ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ፕሮጀክቶች የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል።


ለፕሮጀክቶቹ የመሰረት ድንጋይ ሲቀመጥ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና ሴክተር ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አክሊሉ ታደሰ እንደገለጹት፣ ባለፉት ስድስት ዓመታት የተከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ተግባራት ውጤት እያመጡ ነው።

በእነዚህ ዓመታት በሕዝብና በመንግስት ትብብር በየዓመቱ በሺዎች ለሚቆጠሩ አቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶች ገንብቶና አድሶ ለማስረከብ መቻሉን ተናግረዋል።

በእዚህም በርካቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለጹት አቶ አክሊሉ፣ በልማት ተግባሩ ከፌዴራል እስከ ክልልና ቀበሌ ድረስ ያሉ ተቋማት ተሳትፎና እገዛ እያደረጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።


በተያዘው የክረምት ወራትም ልማቱን በማስቀጠል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትና ተጠሪ ተቋማት በ33 ሚሊዮን ብር አምስት የገጠር ቤቶችና አንድ ሞዴል ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በጉራፈርዳ ወረዳ እንደሚገነቡ ገልጸዋል።

የሚገነቡት የልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ከፍታ ለማረጋገጥ የድርሻውን የሚወጣ ትውልድ ለመፍጠር ሚና እንዳለውም ጠቅሰዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በበኩላቸው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር የእርስ በርስ መተጋገዝና መደጋገፍ ባህልን እያዳበረ መጥቷል ብለዋል።


በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ሥራዎች ተጨባጭ ለውጦች መመዝገባቸውን ተናግረው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትና ተጠሪ ተቋማቱ ይህን የልማት ስራ ለማጠናከር በመምጣታቸው አመስግነዋል።

በክልሉ የማኅበረሰቡን የኢኮኖሚ አቅም የሚያሳድጉና የምግብ ዋስት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉም ገልጸዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በዘንድሮ የክረምት በጎፈቃድ አገልግሎት ሥራዎች ከ200 በላይ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች እድሳትና ግንባታ ሥራ እንደሚከናወን ገልጸዋል።


የትውልድ ለትምህርት ንቅናቄን በስኬት አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰራ ጠቁመው፣ ግንባታቸው እየተከናወኑ ያሉ ሰባት ሞዴል ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶችን በክረምቱ መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትና ተጠሪ ተቋማት ተወካዮች በጉራፈርዳ ወረዳ በነበራቸው ቆይታ ችግኝ በመትከልም አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026