የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የመንገድ መሰረተ ልማትን ከተለያዩ ዘርፎች ጋር ማስተሳሰር ለፈጣን ኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ ነው - አቶ ዛዲግ አብርሃ

Jul 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 13/2017(ኢዜአ)፦የመንገድ መሰረተ ልማትን ከተለያዩ ዘርፎች ጋር ማስተሳሰር ለፈጣን ኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ መሆኑን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለጹ::

ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በትራንስፎርሜሽን ሊደርሺፕ ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው ።


የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ስልጠናውን መስጠት በጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት መንገድ ለአንድ አገር እድገት እና ብልጽግና ወሳኝ ነው፡፡

የመንገድ ግንባታ ኢኮኖሚን በማሳለጥ፣ ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት አንድን አገር ከድህነት ለማውጣት በሚሰራው ስራ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት አስረድተዋል፡፡

የመንገድ ግንባታ አገልግሎትን ከተገልጋይ በማገናኘት፣ ማህበራዊ አካታችነትን በተግባር በማረጋገጥ በኩል ትልቅ ሚና እንዳለውም አንስተዋል።

የመንገድ ሃይሎች የታሰበላቸውን ውጤት እንዲያስገኙ በተለይ ከዲዛይን እስከ ግንባታ እንዲሁም አጠቃቀሙ ላይ ማተኮር ይገባል ነው ያሉት፡፡

በተለይ እንደ ጤና፣ ትምህርት፣ ንግድ እና ከሌሎች ዘርፎች ጋር በሚገባ የመንገድ ግንባታን ማስተሳሰር ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊ ኢንጂነር አብረሃም አብደላ መንገድ ከምህንድስና አንጻር ብቻ ሳይሆን ከሰዎች ሕይወት ጋር ያለውን መስተጋብር ለመረዳት የቻሉበት ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል።


መንገዶችን ስንሰራ አንድ አካባቢን ከሌላው ጋር ከማገናኘት ባለፈ ያሉትን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች አልቆ መገንዘብ እንደሚገባ ከስልጠናው የተገነዘቡበት መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ኢንጂነር አንድነት ሰይፉ ናቸው፡፡

ሰልጣኞቹ የተሰጠው ስልጠና ከሙያዊ እይታ ባሻገር ለአገር ከሚያስገኘው ፋይዳ ጋር አስተሳስሮ ማየት አስችሎናል ብለዋል።


ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች የትራንስፎርሜሽን ሊደርሺፕን በተመለከተ ስልጠና ከትናንት ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026