
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 13/2017(ኢዜአ)፦የመንገድ መሰረተ ልማትን ከተለያዩ ዘርፎች ጋር ማስተሳሰር ለፈጣን ኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ መሆኑን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ገለጹ::
ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በትራንስፎርሜሽን ሊደርሺፕ ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው ።

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ስልጠናውን መስጠት በጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት መንገድ ለአንድ አገር እድገት እና ብልጽግና ወሳኝ ነው፡፡
የመንገድ ግንባታ ኢኮኖሚን በማሳለጥ፣ ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት አንድን አገር ከድህነት ለማውጣት በሚሰራው ስራ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት አስረድተዋል፡፡
የመንገድ ግንባታ አገልግሎትን ከተገልጋይ በማገናኘት፣ ማህበራዊ አካታችነትን በተግባር በማረጋገጥ በኩል ትልቅ ሚና እንዳለውም አንስተዋል።
የመንገድ ሃይሎች የታሰበላቸውን ውጤት እንዲያስገኙ በተለይ ከዲዛይን እስከ ግንባታ እንዲሁም አጠቃቀሙ ላይ ማተኮር ይገባል ነው ያሉት፡፡
በተለይ እንደ ጤና፣ ትምህርት፣ ንግድ እና ከሌሎች ዘርፎች ጋር በሚገባ የመንገድ ግንባታን ማስተሳሰር ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የስልጠናው ተሳታፊ ኢንጂነር አብረሃም አብደላ መንገድ ከምህንድስና አንጻር ብቻ ሳይሆን ከሰዎች ሕይወት ጋር ያለውን መስተጋብር ለመረዳት የቻሉበት ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል።

መንገዶችን ስንሰራ አንድ አካባቢን ከሌላው ጋር ከማገናኘት ባለፈ ያሉትን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች አልቆ መገንዘብ እንደሚገባ ከስልጠናው የተገነዘቡበት መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ኢንጂነር አንድነት ሰይፉ ናቸው፡፡
ሰልጣኞቹ የተሰጠው ስልጠና ከሙያዊ እይታ ባሻገር ለአገር ከሚያስገኘው ፋይዳ ጋር አስተሳስሮ ማየት አስችሎናል ብለዋል።

ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች የትራንስፎርሜሽን ሊደርሺፕን በተመለከተ ስልጠና ከትናንት ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026