የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ለትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስረከብ መሰረት በመሆኑ ህዝቡ የጀመረውን ተሳትፎ ማጠናከር አለበት - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

Jul 31, 2025

IDOPRESS

ሁምቦ፤ ሐምሌ 24/2017(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር ለትውልድ የተሻለች ሀገርን ለማስረከብ መሰረት በመሆኑ ህዝቡ የጀመረውን ተግባር አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወላይታ ዞን ሁምቦ ወረዳ ሶልኳ ተራራ ላይ የዘንድሮን የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አስጀምረዋል።


በዚህን ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተራቆቱ ቦታዎችንና ተራሮችን ለማልማት የተጀመረው ሥራ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተጀመረው ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ተግባር ኢትዮጵያን በዓለም ምሳሌ እያደረጋት መሆኑንም ገልጸዋል።

ችግኝ መትከል የመሬት ለምነትን ከማስጠበቅ፣ ድርቅን ከመከላከልና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከሚኖረው ፋይዳ ባለፈ ለወጣቶች የሥራ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

በወላይታ ዞን ሁምቦ ወረዳ ሶልኳ ተራራ ዛሬ የተተከሉ ችግኞች ከግብ እንዲደርሱ ሁሉም ሰው የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ኃላፊነቱን እንዲወጣ አስገንዝበዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ(ዶ/ር) በበኩላቸው በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።

የተራቆቱ ተራሮችን ለመታደግ የአካባቢው ህዝብ ለአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር ስኬታማነት መረባረብ አለበት ሲሉም ኃላፊው ተናግረዋል።

ችግኝ መትከል ያለውን ጠቀሜታ የተረዳ ማህበረሰብ የመፍጠር ውጥን ከግብ እየደረሰ ስለመሆኑ የዛሬው መርሃ ግብር ማሳያ ነው ብለዋል።

የተፈጥሮ ሚዛንን ለማስጠበቅ የተጀመረው ይህ ሥራ የሁል ጊዜ ተግባር ሆኖ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስገንዝበዋል።

የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር ከተጀመረ ወዲህ በዞኑ የተመናመኑ ደኖችና ተራሮች ለምተው ለኑሮ ምቹ አካባቢ እየተፈጠረ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሰማ ናቸው።

የአየር ንብረት መዛባትን በመቋቋም ለነገው ትውልድ የለማች ሀገር ለማስረከብ መሰረት ለሆነው የአረንጓዴ ልማት መጠናከር ህብረተሰቡ እያደረገ ያለውን ንቁ ተሳትፎ እንዲያጠናክርም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026