የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የቻይና አፍሪካ የዲጂታል ኢኮኖሚ ትብብር የአህጉሪቱን ዕድገት በማሳለጥ ለዜጎች ተጠቃሚነት መሠረት እየጣለ ነው

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የቻይና አፍሪካ የዲጂታል ኢኮኖሚ ትብብር የአህጉሪቱን ዕድገት በማሳለጥ ለዜጎች ተጠቃሚነት መሠረት እየጣለ መሆኑን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን(ኢሲኤ) ገለጸ።

''ቻይና ለአፍሪካ ኢንዱስትሪ፣ ለአረንጓዴና ዘላቂ ልማት ድጋፍ ታደርጋለች’’ በሚል መሪ ሀሳብ በቻይና የአፍሪካ ኅብረት ተልዕኮ፣ የውይይት የጥናትና ትብብር ማዕከል እና በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ (POA) ትብብር የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።


በተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን(ኢሲኤ) የማክሮ ኢኮኖሚ፣ የፋይናንስና አስተዳደር ዳይሬክተር ስቴቨን ካሪንጊ(ዶ/ር)፤ ቻይና ለአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ ድጋፍ እያደረገች ነው ብለዋል።

የቻይና አፍሪካ የኢንዱስትሪና ዲጂታላይዜሽን ልማት ትብብር ለአህጉሪቱ ምጣኔ ሃብታዊ ዕድገት መሳለጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም አስረድተዋል።

በቀጣይም የአፍሪካን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማሳለጥ ቻይና በኃይል አቅርቦት፣ በመሠረተ ልማት ግንባታና በሰው ሃብት ልማት የምታደርገውን ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

በቻይና አፍሪካ ልማት ፈንድ የኢትዮጵያ ቢሮ ተወካይ ሊ ሺባኦ፤ ቻይና ስትራቴጂክ የልማት አጋርነት ዕቅድ በመቅረጽ ለአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬት ቀጣይነት ያለው ድጋፍ እያደረገች ነው ብለዋል።


በዚህም የቻይና ባለሃብቶች የአህጉሪቱን ዘላቂ ዕድገት የሚያሳልጥ መዋዕለ ነዋይ ፈሰስ በማድረግ ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረጉ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

በቻይና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ አካዳሚ የደህንነት ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ሊዩ ዩኢ፤ የቻይና አፍሪካ የዲጂታል ኢኮኖሚ ትብብር በስኬታማ ምዕራፍ ላይ ይገኛል ብለዋል።


የቻይና አፍሪካ የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር ግንባታ ትብብርም በሁሉም የኢኮኖሚ መስክ የአህጉሪቱን ዕድገት ለማስቀጠል መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።

በመድረኩ የቻይና የሥራ ኃላፊዎች የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የዘርፍ ኮሚሽነሮችና የተጋባዥ ተቋማት እንግዶች ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026