የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በጎንደር ከተማ የተከናወኑ እና እየተከናወኑ የሚገኙ ሜጋ የልማት ፕሮጀክቶች የከተማውን ዳግም ትንሳኤ የሚያበስሩ ናቸው - ነዋሪዎች

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር፤ ጥቅምት 30/2018(ኢዜአ)፦ በጎንደር ከተማ በመንግስት ልዩ ትኩረት የተከናወኑ እና እየተከናወኑ የሚገኙ ሜጋ የልማት ፕሮጀክቶች የከተማውን ዳግም ትንሳኤ የሚያበስሩና ወደ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የሚያሻግሩ ናቸው ሲሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም በመገምገም የጥገናና እድሳት ሥራው የተጠናቀቀውን ታሪካዊውን የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት ለጉብኝት ክፍት ማደረጋቸው የሚታወስ ነው።

አስተያየተቻውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማው ነዋሪዎች የለውጡ መንግስት ሌት ተቀን በመስራት ሀገር የሚለውጡና የሚቀይሩ ትጉህና ታታሪ መሪዎችን በተግባር አሳይቷል ብለዋል፡፡

ከከተማው ነዋሪዎች መካከል መራ አብተው እንደገለጹት በጠቅላይ ሚኒስትሩ አመራር ሰጪነት በከተማው የተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች የስልጣኔ፣ የኪነ ሕንጻና የኪነ ጥበብ ማዕከል የሆነችው ጎንደርን ዳግም ታሪኳን ያደሰ ነው፡፡


በኢትዮጵያ የመንግስትነት ታሪክ የተለያዩ መሪዎች ወደ ስልጣን ቢመጡም የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስትን ቅርስ በማደስም ሆነ በመጠገን ከገጠመው የህልውና አደጋ የታደጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ብቻ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል፡፡

ዓለም አቀፍ ቅርስ የሆነው የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት እድሳትና ጥገና ሥራ ታሪክን ከመጥፋት የታደገና የጎንደርንም ዘመናት የዘለቀ ገናና ስምና ታሪክ የሚያስቀጥል ነው ያሉት ደግሞ አድማሴ ደሞዝ የተባሉ ነዋሪ ናቸው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጎንደር በዳግም ውልደት ላይ ትገኛለች እንዳሉት ይህን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከዳር በማድረስ ትንሳኤዋን ለማብሰር ከመሪዎቻችን ጎን በመቆም ታሪክ ለመስራት ዝግጁ ነን ብለዋል።

መገጭ የመስኖና የመጠጥ ውሃ ግድብ ካጋጠሙት ውስብስብ ችግሮች ተላቆ አሁን ላይ በጥሩ የግንባታ አፈጻጸም ደረጃ ላይ እንዲደርስ በማድረግ በኩል የጠቅላይ ሚኒስትሩ የአመራር ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡


በከተማዋ በህዝብ ተሳትፎ ጭምር እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማውን ገጽታ የቀየረና የቱሪስት ፍሰት እንዲጨምር ያደረገ ነው ያሉት ደግሞ ፍሰሃ አዳነ የተባሉ የከተማዋ ነዋሪ ናቸው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና አመራራቸው ለጎንደር ልማትና እድገት የሰጡት ከፍተኛ ትኩረት ቃልን በተግባር ያሳየ ከመሆኑም በላይ በህዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ደስታ መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡

በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ ተስፋ ሰጪ ሜጋ ፕሮጀክቶች በአካባቢው በሰፈነው ሰላም የተገኙ እድሎች በመሆናቸው የልማት ሥራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ለአካባቢያችን ዘላቂ ሰላም የድርሻዬን ለመወጣት ዝግጁ ነው ብለዋል።

በጎንደር ከተማ የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆነው የቆዩት የመገጭ የመስኖና የመጠጥ ውሃ ግንባታ እንዲሁም የአዘዞ ጎንደር የኮንክሪት አስፓልት መንገድ ግንባታ ዳግም ሥራቸው እንዲጀመር መደረጉ የሚታወቅ ነው፡፡

የኮሪደር ልማት ሥራው የከተማውን ገጽታ ከማሳደግ ባለፈ እድገትን በማፋጠንና ምቹ አካባቢን በመፍጠር ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ከተማ እንድትሆን በማድረግ በኩል የጎላ ሚና አለው።

ትኩረት ተነፍጎት የቆየው የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስትን ከህልውና አደጋ ወጥቶ አሁን ላይ ለትውልድ በሚሻገር መልኩ የእድሳትና ጥገና ሥራው ተጠናቆ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በይፋ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ይታወሳል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026