የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የምርምር ማዕከሉ የሩዝ ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራ ነው

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ህዳር 30/2018 (ኢዜአ)፡-የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል የተሻሻሉ የሩዝ ዝርያዎችን በማላመድ የሩዝ ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የሩዝ ልማት ዕድገትን አስመልክተው ሲናገሩ በኢትዮጵያ ሩዝ በፎገራ አካባቢ ይመረት እንደነበረና ምርቱም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የዘለለ እንዳልሆነ ጠቁመዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ማብራሪያቸው በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ከ63 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሩዝ እየተመረተ መሆኑን መግለፃቸውም የሚታወስ ነው።

በአሁኑ ወቅት ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት ምርት በማይካሄድባቸው እንደ ሶማሌ ክልል ባሉ አካባቢዎች ሩዝ በስፋት እየለማ ይገኛል። መንግስት ለልማቱ ትኩረት በመስጠቱም በቅርብ ዓመታት ውስጥ ምርቱ ከተጠቀሰውም እንደሚልቅ ማሳያዎቹ በርካታ ናቸው።


የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከልም የተሻሻሉ የሩዝ ዝርያዎችን በማላመድ የሩዝ ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።

የምርምር ማዕከሉ ቀደም ሲል በሩዝ ምርት በማይታወቁት በደቡብ ኦሞና በአሪ ዞኖች የተሻሻሉ አዳዲስ የሩዝ ዝርያዎችን በማላመድ ለአርሶና አርብቶ አደሩ እያስተዋወቀ ይገኛል።

የምርምር ማዕከሉ ዳይሬክተር ተክሌ ዮሴፍ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለፁት አርሶ አደሩ ከተለመደ የአመራረት ዘይቤ ተላቆ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ግብርናውን እንዲያዘምን በሳይንሳዊ ጥናት የታገዘ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

አካባቢው ለሩዝ ምርት ተስማሚ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፥ በቀጣይም ሩዝ እንደ ሌሎች ሰብሎች በቋሚነት ማልማት እንዲቻል ማዕከሉ የዘር ብዜት ስራውን በስፋት እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

በአካባቢው ያለውን ፀጋ እና ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ከውጭ የሚገባውን የሩዝ ምርት ለመተካት እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል ።


በምርምር ማዕከሉ የሰብል ተመራማሪ አወቀ ታደሰ በበኩላቸው ማዕከሉ በ10 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ የሩዝ ዝርያዎችን ሲያላምድ መቆየቱን ጠቁመዋል ።

ማዕከሉ ካላመዳቸው የሩዝ ዝርያዎች "ዕድገት'' ፣ ''ፎገራ-1" እና ''ፓዌ -2" የተሰኙ የሩዝ ዝርያዎች ለአካባቢው ስነ-ምህዳር ተስማሚና በሄክታር እስከ 78 ኩንታል ምርት መስጠት የሚችሉ በመሆናቸው ተመራጭ አድርጓቸዋል ብለዋል።

በተለይ እነዚህ የሩዝ ዝርያዎች በአጭር ጊዜ ሊደርሱ የሚችሉ እና በበሽታና በተባይ የማይጠቁ በመሆናቸው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

እስካሁን በደቡብ ኦሞ ዞን በግብርና ኢንቨስትመንት በተሰማሩ ባለሃብቶች በ230 ሄክታር መሬት ላይ በሙከራ ደረጃ የለሙ የሩዝ ዝርያዎች ውጤታማ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

በዘርፉ የተሰማሩ የግል ባለሀብቶች የሩዝ ዝርያዎችን በስፋት ቢያለሙ በውጪ ምንዛሬ ከውጭ የሚገባውን የሩዝ ምርት በአገር ውስጥ ምርት መተካት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡

በደቡብ ኦሞ ዞን በናይ ጸማይ ወረዳ በግብርና ልማት ላይ የተሰማሩት አቶ ወርቁ ሮሮ፣ ከጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል ባገኙት የዘርና የክህሎት ድጋፍ በሙከራ ደረጃ በ3 ሄክታር መሬት ላይ ሩዝ ማልማታቸውን ጠቁመዋል።

በዚህም 130 ኩንታል የሩዝ ምርት ማግኘታቸውን ጠቅሰው የሩዝ ምርት አዋጭና ጊዜና ጉልበት ቆጣቢ መሆኑን ጠቅሰው በ10 ሄክታር ላይ ለዘር ብዜት የሚሆን ሩዝ እያመረቱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በቀጣይም የጀመሩትን የሩዝ ልማት ስራ የማስፋፋት ዕቅድ እንዳላቸውም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026