የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተከናወኑ ተግባራት ሀገር ወደተሻለ ከፍታ እንድታመራ መሰረት ጥለዋል

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ፤ ጥር 3/2018 (ኢዜአ)፡-በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የተከናወኑ ተግባራት ሀገሪቱ ወደተሻለ ከፍታ እንድታመራ መሰረት የጣሉ መሆናቸውን የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ።

ስትራቴጂው በቅርቡ ይፋ የተደረገውን ዲጂታል 2030 ትግበራን ለማሳካት ትልቅ ግብዓት እንደሚሆንም ምሁራኑ ጠቁመዋል።

መንግስት የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ በየዘርፉ የጀመራቸውን ሥራዎች ይበልጥ ለማዘመንና ለማሳለጥ በቅርቡ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

ምሁራኑ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተተገበሩ ቴክኖሎጂዎች ሀገሪቱ ወደተሻለ ከፍታ እንድታመራ መሰረት የጣሉ ናቸው።

ዲጂታል ቴክኖሎጂው በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርትና በፋይናንስ ዘርፎች ያመጣው ተጨባጭ ለውጥና ያስገኘው ጥቅም እያደገ መሆኑን የተናገሩት በዩኒቨርሲቲው የሶፍት ዌር ኢንጂነሪንግ መምህር በላይ አለምነህ ናቸው።

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ስኬቶች በዘርፉ ልምድና ተሞክሮ የተቀሰመበት መሆኑን ገልጸው፣ በስትራቴጂው በተዘረጉ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶች በተለያዩ ተቋማት ከወረቀት ነጻ የሆነ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተናግረዋል።

በዩኒቨርሲቲውም የትምህርት መርሃ ግብሮችና በሥራ ክፍሎች የመረጃ ልውውጥ ሥራው ከወረቀት ነጻ በሆነ መንገድ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዞ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱ በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በመደረጉ ተማሪዎች ጊዜና ቦታ ሳይገድባቸው ትምህርታቸውን በኦንላይን መከታተል መቻላቸውን ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ ተቋማት እና ግለሰቦች ጋር የሚያደርገው ግንኙነትና የተማሪዎች ውጤትም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደራሽ መደረጋቸውንም ነው ያመለከቱት።

የመማር ማስተማር ሂደቱን በማዘመንና የፈተና አሰጣጥ ሥርአቱን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የፈተናን ደህንነት ለማስጠበቅ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም አስረድተዋል።

በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የተከናወኑ ስኬታማ ተግባራት በቅርቡ ይፋ ለተደረገው ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ መሰረትና ግብአት መሆናቸውን ተናግረዋል።

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኔትዎርኪንግ ሳይበር ደህንነት መምህር ወንድወሰን ዝና በበኩላቸው ለተማሪዎች በሳይበር መረጃ ደህንነት አጠባበቅ ላይ በተግባር የተደገፈ ትምህርት ለመስጠትና በቂ ዕውቀት ለማስጨበጥ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 አበርክቶ ላቅ ያለ መሆኑን ተናግረዋል።

በየደረጃው ለትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ይበልጥ መረጋገጥ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸው፣ "ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠል በዲጂታል ቴክኖሎጂ ያሉ አማራጮችን በአግባቡ ልንጠቀምባቸው ይገባል" ብለዋል።

ስትራቴጂው ዜጎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ አማራጮች ታግዘው ባሉበት ቦታ ትምህርታቸውን መከታተል የሚችሉበት ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም ጠቁመዋል።

እንደ መምህሩ ገለጻ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ተግባራዊ መሆን እንደሀገር ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ከመከላከል ባለፈ የተለያዩ ማጭበርበሮችን ለማስቀረትም እያገዘ ነው።

ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ አካታችና ተደራሽ እንዲሆን በማድረግ በሁሉም ዘርፍ ተግባራትና የሚሰጡ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ የታገዙና ቀልጣፋ እንዲሆኑ የተጀመሩ ሥራዎች መጠናከር እንዳለባቸውም መምህሩ ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026