የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የገጠር መንገድ ግንባታው የአርሶአደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የበለጠ የሚያረጋግጥ ነው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር ፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል እየተከናወነ ያለው የገጠር መንገድ ግንባታ የአርሶአደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የበለጠ ለማረጋገጥ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ዑመር ገለጹ።

በሐረሪ ክልል ገጠሩን ከከተማ የሚያስተሳስር የ150 ኪሎ ሜትር የመንገድ ግንባታና ጥገና እየተከናወነ ይገኛል።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር ለኢዜአ እንዳሉት፣ የገጠር መንገድ ግንባታው፣አርሶአደሩ ምርቱን በቀላሉ ወደ ገበያ እንዲያቀርብ ያግዛል።

የአርሶአደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የበለጠ ለማረጋገጥ የጎላ ሚና እንደሚኖረውም አንስተዋል።

በክልሉ የኢንቨስትመንት ፍቃድ የወሰዱ አልሚዎች የስራ እንቅስቃሴን በጥብቅ ዲሲፕሊን መምራት ይገባል

በከተማዋ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ከገጠሩ ጋር በማስተሳሰር ሞዴል የገጠር መንደሮችን ለመገንባት እየተደረገ ያለውን ጥረት እንደሚያግዝም ነው ያነሱት።

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ፈቲህ ተውፊቅ በበኩላቸው፣ በተያዘው በጀት ዓመት በክልሉ ገጠርን ከከተማ የሚያስተሳስሩና የህብረተሰቡን ኑሮ የሚያሻሽሉ የመንገድ መሰረተ ልማቶች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


የአዳዲስ የገጠር መንገዶች ግንባታን ጨምሮ ነባሮቹን የማሻሻልና ሥራ በተያዘለት የጊዜ ገደብ በጥራት እንዲጠናቀቅም ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው፤ የመንገዱ ግንባታ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንደሚሰጣቸው ገልጸው፤ ለግንባታው አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።


ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የድሬ ጠያራ ወረዳ ሲጊቻ ቀበሌ ነዋሪ ሐሰን ዩስፌ፤ ምርታቸውን ከተማ ይዘው በመሄድ እንዲገበያዩና የተሻለ ጥቅም እንዲያገኙ የመንገዱ ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።


ፉአድ ሙሳ በበኩላቸው፤ቀደም ሲል የነበረው መንገድ ጠባብና ለተሽከርካሪ ምልልስ አስቸጋሪ እንደነበር አስታውሰው፤ አዲስ እየተገነባ ያለው መንገድ ይህን ችግር በማቃለል የተሽከርካሪ ፍሰቱን ያሳልጣል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026