የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ወደ ላቀ ውጤታማነት አሸጋግሯል

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 14/2018 (ኢዜአ)፦የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ወደ ላቀ ውጤታማነት ማሸጋገሩን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መለሠ መና ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የሀገሪቱን ቁልፍ የመንግሥትና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማትን ያሰባሰበው “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” ኮንፈረንስ መካሄዱ ይታወሳል።

በኮንፈረንሱም በኢትዮጵያ ኢንቨትመንት ሆልዲንግስ ስር የሚገኙ የልማት ድርጅቶች የነበረባቸውን የፋይናንስ፣ የኦዲት፣ የካፒታል፣ የብድር ጫና እና የኮርፖሬት አስተዳደር ችግር በመቅረፍ ዘመናዊ የባለቤትነት፣ የአስተዳደር ስርዓት እና ዓለም አቀፍ የኮርፖሬት አስተዳደር ስርዓት እንደተዘረጋላቸው ተገልጿል።

ዘመናዊ የኦዲት ስርዓት እንዲከተሉ መደረጉን እና ይህም ካጋጠማቸው የኢኮኖሚ ስብራት ወጥተው በፍጥነት ውጤታማ እንዲሆኑ አስቸሏል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መለሠ መና ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከ40 በላይ የመንግስት ልማት ድርጅቶች መኖራቸውን ተናግረዋል።

ቋሚ ኮሚቴው ድርጅቶቹን ከተሰጣቸው ተልዕኮና ስትራቴጂካዊ ዕቅድ አንጻር የመከታተል፣ የመቆጣጠርና የመደገፍ ስራ በማከናወን ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በለውጡ መንግሥት የተደረገውን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ተከትሎ የልማት ድርጅቶች ከነበሩበት ኪሳራ ወጥተው ወደ ትርፋማነት መሸጋገራቸውን አንስተዋል።

የልማት ድርጅቶቹ ተኪ ምርት በማምረት ከውጭ የሚገባ ምርት መጠን እንዲቀንስ፣ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ እና ለዜጎች የስራ እድል እንዲፈጠር በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና እያበረከቱ ነው ብለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅትም ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት እና ለቀጣይ ትውልድ መሸጋገር የሚችል ሃብት በመፍጠርና በማፍራት ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡


የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሀብታሙ ኃይለሚካኤል በበኩላቸው፣ ከለውጡ በፊት አብዛኛዎቹ የልማት ድርጅቶች ዘመናዊ አሰራርን ባለመከተላቸው ለኪሳራ ተዳርገው መቆየታቸውን አስታውሰዋል።

የለውጡ መንግስት የተከተለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ድርጅቶቹ ያለባቸውን ዕዳ በማቃለልና ከኪሳራ እንዲወጡ በማድረግ በዘርፉ ተጨባጭ ለውጦችን አምጥቷል ነው ያሉት፡፡

በዚህም ድርጅቶቹ የሃብት አማራጮችን በማስፋት በኢኮኖሚ እድገት ውስጥ ጉልህ ሚና ለመጫወት ትኩረት ሰጥተው በመስራት ላይ ይገኛሉ ብለዋል ፡፡

በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሥር የሚተዳደሩ የልማት ድርጅቶች ከአጠቃላይ ሀገራዊ ምርት ውስጥ የ12 በመቶ ድርሻ ያላቸው ሲሆን ከፍተኛ ታክስ ከፋዮች መሆናቸውን አንስተዋል።

ለአብነትም በ2017 በጀት ዓመት ከ228 ቢሊዮን ብር በላይ ለመንግስት ታክስ መክፈላቸውን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026