🔇Unmute
ጎንደር ፤የካቲት 3/2018(ኢዜአ)፦ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) ቴክኖሎጂን ተጠቅመው ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሃይል የሚያፈሩበት ዕድል መፈጠሩን የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
ኢንስቲትዩቱ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂውን ለማስተዋወቅና ተደራሽነቱን ለማስፋት ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራርሟል።
ሥምምነቱን የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ይታገሱ ደሳለኝና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ፈርመውታል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስኢንስቲትዩትምክትል ዋና ዳይሬክተር ይታገሱ ደሳለኝ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኢትዮጵያ የምትፈልገውን የሰለጠነ የሰው ሃይል እንዲያፈሩ የአቅም ግንባታ ላይ የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ ነው።
ከተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡ የሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች ኢንስቲትዩቱ በሚያደርግላቸው ድጋፍ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ የመመረቂያ ጥናታቸውን እያካሄዱ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢንስቲትዩቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት በመታገዝ አምስት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን ማበልጸጉን ጠቅሰው፣ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ዘርፉን ለጥናትና ምርምር የበለጠ እንዲጠቀሙበት ጠይቀዋል።

የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን እውን ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንዳለው የተናገሩት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ ቴክኖሎጂው ለብዝሃ-ዘርፎች ዕድገት ወሳኝ ሚና ይጫወታል ብለዋል።
ጎንደር ዩንቨርሲቲ በጤናው ዘርፍ ያለውን የካበተ ልምድ በሰው ሰራሽ አስተውሎት በማስደገፍ የጤና መረጃ ሥርዓትን የበለጠ ሊያዘምን ይገባል ብለዋል።
የጎንደር ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የሰለጠነ የሰው ሃይል ለማፍራት በዘርፉ አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞችን ከፍቶ ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቋል ብለዋል።

የሰው ሰራሽ አስተውሎት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን ለማካሄድ አዎንታዊ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
ዩንቨርሲቲው በሰው ሰራሽ አስተውሎት የምርምር ማዕከል በማቋቋም ከሀገር ባለፈ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የመሆን ግብ ይዞ እየሰራ እንደሆነም አስረድተዋል።
ስምምነቱ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ከመጠቀም ባለፈ ኢትዮጵያ የራሷን ቴክኖሎጂ ማበልጸግ የሚያስችላትን ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም አንስተዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026