🔇Unmute
ቦንጋ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በዘንድሮው የበልግ ወቅት ከ415 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት እየለማ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መሥተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ማስረሻ በላቸው በሰጡት መግለጫ፤ በዘንድሮው የበልግ ወቅት በዋና ዋና ሰብሎች ብቻ ከ415 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በማልማት ከ16 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ ነው።

ለዚህም የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር መቅረቡን ገልጸው፤ የድጋፍና ክትትል ሥራውም በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ለማልማት ከታቀደው ውስጥ እስካሁን 373 ሺህ 475 ሔክታሩ መታረሱንና 126 ሺህ ሔክታሩ ደግሞ በዘር መሸፈኑን አብራርተዋል።
በአጠቃላይ ከሚለማው ውስጥም ከ124 ሺህ ሔክታር የሚልቀውን በክላስተር ለማልማት ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን በተመለከተ፤ በክልሉ ከለማው 5 ሺህ 700 ሔክታር ማሳ ከ2 ሺህ ሔክታር ከሚበልጠው ማሳ ላይ የነበረው ምርት መሰብሰቡን አስታውቀዋል።
በመስኖ ከለማውና በአትክልት፣ በፍራፍሬ እንዲሁም በሌሎች የሆርቲካልቸር ሰብሎች ከተሸፈነው ከ51 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት 11 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ ጠቁመው፤ እስካሁን 9 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል።
አርሶ አደሩ አሁን ያለውን ምቹ የአየር ሁኔታ ተጠቅሞ የእርሻ ሥራውን በወቅቱ እንዲያከናውን አሳስበዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026