የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በጋምቤላ ክልል የነዳጅ ግብይትና ስርጭት መመሪያ ተግባራዊ እየተደረገ ነው

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ) ፦በጋምቤላ ክልል የነዳጅ ግብይትና ስርጭት መመሪያን ተግባራዊ በማድረግ በህዝቡ ላይ ሊደረሱ የሚችሉ ጫናዎችን ለመቀነስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ የነዳጅ ስርጭትና ግብይት መመሪያ ትግበራን ለማሳለጥና ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለመቆጣጠር በክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የሚመራ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።

የጋምቤላ ክልል ንግድና እንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኮንግ ኩላንግ ለኢዜአ እንደገለጹት በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰተውን አለመረጋጋት ተከትሎ በህዝብ ላይ ሊደርስ የሚችለውን ጫና ለመቀነስ እንደ ሀገር የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት መመሪያ ተላልፏል።

በክልሉ ለነዳጅ አመላላሽ ቦቴዎች፣ የምግብ ፍጆዎችንና ሸቀጦችን ለሚጭኑና ለህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ለሚሰጡ ተሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠት የማስተናገድ ተግባር እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

እንዲሁም በግብርና ልማት ስራ የሚሰማሩ ትራክተሮችና ሌሎች ተሽከርካሪዎች እየተስተናገዱ እንደሚገኙም ተናግረዋል።

በክልሉ እየተተገበረ የሚገኘውን ይህንኑ የነዳጅ ስርጭትና ግብይት ለማሳለጥና ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለመቆጣጠር በክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የሚመራ ሰባት የፌዴራልና የክልል ተቋማት የተካተቱበት ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑንም ኃላፊው ገልጸዋል።

የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ከሚሰጡ አሽከርካሪዎች መካከል አቶ ጋሻው ተፈራና አብዱልፈታ አህመድ በሰጡት አስተያየት መንግስት ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን ታሳቢ በማድረግ ያስተላለፈው የነዳጅ ግብይትና ስርጭት መመሪያ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ በማደያዎች ከታሪፍ ጀምሮ የአተገባበር ክፍተቶች መኖራቸውን ጠቁመው በመንግስት የተላለፈ የነዳጅ ስርጭትና ግብይት መመሪያ ሳይሸራረፍ በአግባቡ ስራ ላይ ሊውል ይገባል ብለዋል።

የጋምቤላ ከተማ የስፖርት ነዳጅ ማደያ ተወካይ አቶ አዲሱ አሰፋ እንደገለጹት በማደያቸው ከንግድ ቢሮ በሚሰጠው መመሪያ መሰረት ተሽከርካሪዎችን እያስተናገዱ ይገኛሉ።

ታሪፉን በተመለከተም መንግስት ባወጣው የዋጋ ተመን መሰረት እየሸጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026