የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በሲዳማ ክልል በቴክኖሎጂ በመታገዘ ገቢን በአግባቡ ለመሰብሰብ ተችሏል - ባለስልጣኑ

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ሚያዚያ 8/2018 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል በቴክኖሎጂ በመታገዘ ገቢን በአግባቡ ለመሰብሰብ መቻሉን የክልሉ ገቢዎች ባለስልጣን አስታወቀ።

የባለስልጣኑ ምክትል ዳይሬክተርና የደንበኞች አገልግሎት፣ የታክስ አወሳሰንና አሰባሰብ ዘርፍ ኃላፊ ሙላት ዮሴፍ ለኢዜአ እንደገለጹት ፤ በክልሉ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን በማዘመን ውጤታማ ስራዎችን ለመስራት እየተቻለ ነው።

የክልሉን ገቢ ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ሲሆን ዘመናዊ የአከፋፈል ስርዓት (የኢ-ፋይልንግና የኢ-ፔይመንት) አሰራር መዘርጋቱ ለውጤቱ አስተዋጽኦ ከማድረግ ባለፈ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል ነው ያሉት።

በተለይም ከእጅ ንክኪ ነጻ የሆነ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን በማዘመን ክልሉ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ ለመሰብሰብ አስችሏል ብለዋል።

በተለይም ከፍተኛ ግብር ከፋይ የሆኑ ከ626 በላይ የመንግስትና የግል ተቋማት ሙሉ በሙሉ ግብራቸውን የሚያሳውቁበትና የሚከፍሉበት የኤሌክትሮኒክስ አሰራር ነው የተዘረጋው ብለዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት ለመሰብሰብ ከታቀደው ከ 21 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ውስጥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ15 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማግኝት መቻሉን ገልፀዋል።

የተሰበሰበው ገቢ የእቅዱን 94 በመቶ ለማሳካት ያስቻለ ሲሆን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

ገቢው ከመደበኛና ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች የተሰበሰበ መሆኑንም ተናግረዋል።

በፌዴራል ደረጃ የተሻሻለው አዲሱን የግብር አዋጅ ጨምሮ ሌሎች የታሪፍ ማሻሻያዎች መደረጋቸው የገቢ አቅምን ለማሳደግ የራሱ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል፡፡

በዚሁ ወቅት የቁጥጥርና የአሰራር ስርዓትን በማጠናከር ለታክስ ህግ ተገዥ ባልሆኑ ከ400 በላይ ግብር ከፋዮችን ጨምሮ በክልሉ ሰባት ከተሞች ደረሰኝ ሳይቆርጡ በሚሰሩ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል፡፡

በቀሪ ጊዜትም የተቀመጠውን እቅድ ለማሳካት ወቅታዊ ሁኔታን ያገናዘበ የክትትልና የቁጥጥር ስራ እንደሚከናወን ገልጸዋል፡፡


በሃዋሳ ከተማ ግብር ከፋይ የሆኑት መምህር ተስፋዬ አበበ፤ በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አከፋፈል ስርዓት መኖሩ ሂደቱን ቀልጣፋ እንዳደረገው ገልፀዋል።

ግብርን በታማኝነት መክፈል ሀገራዊ ግዴታ በመሆኑ ኃላፊነታቸውን በተገቢው እየተወጡ መሆኑን አመልክተው ድርጅታቸው ላለፉት ተከታታይ ዓመታት የክልሉ ከፍተኛ ግብር ከፋይ በመሆን ሽልማት ማግኘቱን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026