የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የዲጂታል አሰራርን በማዘመን የመረጃ ማረጋገጥና ማደራጀት ተግባር ይጠናከራል

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፣ሚያዚያ 12/2018(ኢዜአ)፡- የዲጂታል አሰራርን በማዘመን መረጃን የማረጋገጥና የማደራጀት ተግባር እንደሚጠናከር የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር) ተናገሩ።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች የመረጃ ማረጋገጥ ስራን የተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በሰመራ እየተካሄደ ነው።


በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም የአፋር ክልል፣ የዞንና የወረዳ የሰው ሃብት ዳይሬክተሮች እየተሳተፉ መሆኑም ተገልጿል።

በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር) እንዳሉት በዚህ ወቅት የዲጂታል አሰራርን መተግበር አስፈላጊ ነው።

በዚህም የዲጂታል አሰራርን በማዘመንና የሲቪል ሰርቫንቱን መረጃ የማረጋገጥና የማደራጀት ተግባር ሊጠናከር ይገባል ብለዋል።

ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስን እውን ማድረግ ያለው ጠቀሜታ ዘርፈ ብዙ መሆኑን ገልፀው በተደራጁና ዘመኑን ባገናዘቡ መረጃዎች የተሳለጠ የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ማስፈን ላይ በፍጥነት መስራት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ክልሉ ትኩረት ሰጥቶ የሰራተኛውን መረጃ ከዲጂታል መታወቂያ ጋር የማያያዝ ሰራ ተግባራዊ ማድረጉ እንደ አገር የተጀመረውን መረጃን የማዘመንና ዕውን የማድረግ ተግባርን የሚያሳልጥ ነው ብለዋል።

በዚህም መረጃን በማዘመን ስልጡን የሆነ አገልጋይ ሲቪል ሰርቫንትን ማጠናከር ላይ ትኩረት መደረጉን አመልክተዋል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ አህመድ በበኩላቸው ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስን እውን በማድረግ ረገድ እየተከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታ ነው ብለዋል።

ይህም የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ አገዛ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በመድረኩም የአፋር ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክተሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026