የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግርን በማፋጠን ረገድ የላቀ ሚና እየተጫወተ ይገኛል  

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግርን በማፋጠንና የኢንቨስትመንት ስኬትን በማረጋገጥ ረገድ የላቀ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ሀሰን መሐመድ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 25 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆየውን የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኤክስፖ መርቀው መክፈታቸው ይታወቃል፡፡

በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ቀደም ሲል ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ስኬታማ ተግባራት ተመዝግበዋል።

በተለይም የአምራች ኢንዱስትሪዎች አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱና ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ከ2 ሺህ 800 በላይ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ መቻሉ የዘርፉ ዕድገት ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።

በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ በሀገር ውስጥ ተኪ ምርቶች አማካኝነት ከ4 ነጥብ 85 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስረድተዋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ሀሰን መሐመድ እንዳሉትም፣ ኤክስፖው መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግርን በማፋጠን ረገድ ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡

የዘርፉን አስተዋጽኦ ዘላቂ ለማድረግ መሰረታዊ የፖሊሲ ማሻሻያዎችና ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በተለይም በኢንቨስትመንት ረገድ ትልቅ ስኬት መመዝገቡን ገልጸዋል።

ይህም የሀገሪቱን የወደፊት ኢኮኖሚ በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት የሚያስችሉ የፋይናንስና የፖሊሲ ድጋፎች ውጤታማ በሆነ መንገድ እየተተገበሩ መሆናቸውን ያረጋግጣል ብለዋል።

ኤክስፖው የሀገር ውስጥና የውጭ ገበያ ትስስርን በማጠናከር እንዲሁም የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን፣ የኢንዱስትሪውን ዕድገት ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገረ ይገኛል ብለዋል።

በተጨማሪም የውጭ ምንዛሬን በማዳንና ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት፣ በራስ አቅም የመቆም የኢኮኖሚ አርበኝነትን እያረጋገጠ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን በዕውቀትና ክህሎት የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራትም ከተለያዩ የትምህርትና የሥልጠና ተቋማት ጋር በተቀናጀ መልኩ ሰፊ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

ፍጥነትን፣ ፈጠራንና የዝላይ መርህን በመጠቀም በትንሽ ወጪ ከፍተኛ ምርት በማምረት፣ የኢንዱስትሪውን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በኤክስፖው አማካኝነት በርካታ አምራቾች ከግልና ከመንግሥት ተቋማት ጋር ጠንካራ የገበያ ትስስርና የሥራ ስምምነቶችን በመፍጠር ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026