የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አረንጓዴ አሻራ ሀገራዊ የንብ ሃብት መጠንን በማሳደግ የማር ምርትና ጥራት እንዲጨምር ጉልህ አስተዋጾ አድርጓል

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ግንቦት 12/2018 (ኢዜአ)፡-የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ሀገራዊ የንብ ሃብት መጠንን በማሳደግ የማር ምርትና ጥራት እንዲያድግ ጉልህ አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ የንብ ልማት ማህበር አስታወቀ።

ዓለም አቀፍ የንብ ቀን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደረጃ በዲላ ከተማ ሲከበር ኢዜአ ያነጋገራቸው ባለድርሻ አካላት እንዳሉት ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ ለንብ ሃብት ልማት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።

በየዓመቱ የሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብርም፣ ሀገራዊ የንብ ሃብት መጠንን በመጨመር የማር ምርትና ጥራት እንዲያድግ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተገልጿል።

መርሀግብሩ የተፈጥሮ ሚዛንን ከመጠበቅ ባለፈ የሥነ ምግብ ይዘትን ለማሻሻል ጉልህ አስተዋጾ እያበረከተ መሆኑም ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ የንብ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ ነጋሽ በቀና በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ መንግስት ለንብ ሃብት የሰጠው ትኩረት የዘርፉን እምቅ አቅም አውጥቶ ለመጠቀም እያስቻለ ነው።

በተለይ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብርን ጨምሮ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራዎች የንብ ሃብት መጠንን በማሳደግ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ እያገዙ መሆኑን ተናግረዋል።

የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራው ከሌማት ትሩፋት ትግበራ ጋር ተዳምሮ የተፈጥሮ ሚዛንን ከመጠበቅ ባለፈ የማር ምርት ጥራትና ይዘትን አሻሽሏል ብለዋል።

የክልሉን እምቅ የንብ ሃብት ልማት በአግባቡ ለመጠቀም የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ሃላፊና የእንስሳትና አሣ ሃብት ልማት ዘርፍ ሃላፊ አባይነህ ከዳ (ዶ/ር) ናቸው።

በተለይ የንብ መንጋ ብዜት ማዕከላትን በማስፋፋትና አርሶ አደሩን በመንደር በማደራጀት በተደረገ የግብዓትና የክህሎት ድጋፍ የዘርፉን ምርታማነት ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ከ17 ሺህ ቶን በላይ ጥራቱን የጠበቀ ማር ለገበያ መቅረቡን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ የአንድነት ንብ ልማት ማህበር ሰብሳቢ ወይዘሮ ብርቱካን ተስፋዬ በበኩላቸው 12 ሆነው በማህበር በመደራጀት በንብ ልማት ሥራ መሰማራታቸውን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት ማህበሩ ባለው ከ50 በላይ ዘመናዊና ባህላዊ የንብ ቀፎ በዓመት ከ1 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ ማር በማምረት ለገበያ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም የማህበሩ አባላት ከራሳቸው ባለፈ ቤተሰቦቻቸውን በመርዳት ለሌሎች ወጣቶች አርአያ የሚሆን ተግባር እያከናወኑ መሆኑንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026