የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በክህሎት የበለፀገ የሰው ኃይል በማፍራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን እያሳለጠ ነው

May 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ የአምስት ሚሊየን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በክህሎት የበለፀገ የሰው ኃይል በማፍራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን እያሳለጠ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና መርሃ ግብር እስከ አሁን ከ4 ነጥብ 85 ሚሊየን በላይ ሰዎች ስልጠና በመውሰድ የሰርተፍኬት ባለቤት እየሆኑ እንደሚገኝም አስታውቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ስልጠናን ሐምሌ 2016 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው የሚታወስ ነው።

የአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ተነሳሽነት ወጣቶች ላይ ትልቅ ለውጥ ለማምጣት ያለመ የዲጂታል ክህሎት ማልሚያ መርሃ ግብር ሆኖ እያገለገለ ሲሆን በዚህም ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገብ ጀምሯል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግሥት ጋር በመተባበር ያስጀመረው የኢትዮ-የኮደርስ ስልጠናም ሀገራዊ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን በማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።

ስልጠናውም ዜጎች በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ዳታ አናሊሲስ፣ በአንድሮይድና በፕሮግራሚንግ ዴቨሎፕመንት ዋና ዋና ዘርፎች ስልጠና የሚያገኙበትን ምኅዳር ፈጥሯል።

ስልጠናው በኦላይን ሥርዓት በነፃ የሚሰጥና ዜጎች ያለ ዕድሜ ገደብ መሠረታዊ የዲጂታል ስልጠና ወሰደው ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለው ሰርተፍኬት ያገኙበታል።

የዲጂታል ኢኮኖሚ ሥርዓትን በመገንባት ሂደትም በርካታ ዜጎችን የቴክኖሎጂ ክህሎት በማስታጠቅ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል።

ይህም የኢትዮጵያን የግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይሲቲ ብዝኅ የኢኮኖሚ ጉዞ የሚያሳልጥ ሀገር በቀል የዲጂታል ክህሎት የታጠቀ ትውልድ በማፍራት እያስቻለ ነው።

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ስዩም መንገሻ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዲጂታል ኢኮኖሚን መገንባት የሚያስችል ሥነ-ምኅዳር ተፈጥሯል።

ለአብነትም የአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና በርካታ ዜጎች የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት የሚታጠቁበትን አስቻይ የአሰራር ሁኔታ መፍጠሩን አስታውቀዋል።

የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ከተጀመረ አንስቶም እስካሁን ከ4 ነጥብ 85 ሚሊየን በላይ ዜጎች የስልጠናው አካል በመሆን የተለያዩ የዓለም አቀፍ ሰርተፊኬት ባለቤት እየሆኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ለፈጠራና ቴክኖሎጂ ልማት የተሰጠው ትኩረትም የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያሳልጥ የሰው ሃይል ማፍራት እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠናም የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት የታጠቀ ብቁ የሰው ሃይል በማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የስልጠና መርሃ ግብሩም ዜጎች ባሉበት ቦታ ሆነው በኦላይን ሥርዓት ዕውቀት የሚሸምቱበትን ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰዋል።

በቀሪ የሥልጠናው ጊዜያትም ዜጎች የዕድሉ ተጠቃሚ በመሆን የዲጂታል ዕውቀትና ክህሎት ማዳበር እንደሚችሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026