🔇Unmute
ጂማ፣ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ በጂማ ከተማ በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ወጣቶች ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገለጹ።
በከተማዋ የወጣቶችን የሥራ ዕድል ለማስፋት የግብርና፣ የቴክኖሎጂና የንግድ ሥልጠናዎችን በመስጠት፣ የመሥሪያና መሸጫ ቦታዎችን በማቅረብ እንዲሁም የገበያ ትስስር በመፍጠር ረገድ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ።
በከተማዋ ኢዜአ ያነጋገረው ወጣት አብዱረሂም ናስር እንደገለጸው፤ የከተማ አስተዳደሩ ባመቻቸለት የሥራ ዕድል በመጠቀም የዳቦ መጋገሪያ ማሽኖችን በጥራት አምርቶ ለገበያ እያቀረበ ይገኛል።
እነዚህ ማሽኖች ከውጭ የሚገቡ የዳቦ መጋገሪያ ምርቶችን በመተካት የውጭ ምንዛሬን ከማዳናቸው ባለፈ፣ ኃይል ቆጣቢ በመሆናቸው በገበያ ላይ ተመራጭ መሆናቸውን አስረድቷል።
ይህም ገቢውን ከመጨመር ባለፈ ለሌሎች ወጣቶች የሥራ ዕድል እንዲፈጥር እንዳገዘው ጠቁሟል።

በተመሳሳይ ዘመናዊ ቦርሳዎችንና የቆዳ ውጤቶችን በማምረት ለገበያ እያቀረቡ ከሚገኙ ወጣቶች መካከል ደርሶልኝ ሽመልስ እና ሀብታሙ ጋዲሳ ይጠቀሳሉ።
ወጣቶቹ እንደሚያስረዱት፤ የሚያመርቷቸው የቆዳ ውጤቶች በቅርጽም ሆነ በጥራት የሸማቹን ፍላጎት ያሟሉ በመሆናቸው በገበያ ላይ ተወዳዳሪ መሆን ችለዋል።
ሥራቸውን ይበልጥ ለማስፋፋትም የከተማ አስተዳደሩ የብድርና የመሥሪያ ቦታ እንዳመቻቸላቸው ገልጸዋል።
የጂማ ከተማ የሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዱልሀሚድ ኑረዲን በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በከተማዋ ለወጣቶች የሥራ ዕድልን ለማስፋፋት በርካታ የመሥሪያና የመሸጫ ሼዶች ተገንብተዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ከ3 ሺህ በላይ በማኅበራት ለታቀፉ 20 ሺህ 160 ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ፣ ዕቅዱን በማሳለጥ 28 ሺህ 500 ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
የወጣቶቹን ስኬት ይበልጥ ለማገዝ የሥልጠናና የብድር አቅርቦት መመቻቸቱን የገለጹት ኃላፊው፤ በበጀት ዓመቱ እስካሁን 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት መቅረቡን ጠቁመዋል።
ለወጣቶቹ የሥራ ዕድልን ለማስፋፋትም ለቡና መፈልፈያ፣ ለዳቦና እንጀራ መጋገሪያ፣ ለቆዳና እንጨት ሥራዎች እንዲሁም ለሌሎችም ተኪ ምርቶች ማምረቻ የሚሆኑ ሼዶች መሰጠታቸውን አክለዋል።
ወደ ሥራ የገቡት ወጣቶች ምርቶቻቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ ለሕብረተሰቡ ከማቅረብ ባለፈ፣ ተኪ ምርቶችን በማምረት የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻላቸውንም አቶ አብዱልሀሚድ ገልጸዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026