የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የጤና ተቋማትን አገልግሎት ወረቀት አልባ የሚያደርግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ ነው

Jun 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018(ኢዜአ)፦ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የጤና ተቋማትን አገልግሎት ወረቀት አልባ የሚያደርግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ ገለጹ፡፡

ዶክተር ደረጄ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ የልማት አቅጣጫ በጤናው ዘርፍ ፈጣንና ቀልጣፋ የአገልግሎት ምኅዳር በመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ ነው።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂም የጤና ተቋማትን አገልግሎት በማዘመን ወሳኝ መሰረት መጣሉን አስታውሰዋል።

ለአብነትም የጤና ተቋማትን አገልግሎቶች በኦላይን የዲጂታል ሥርዓት በማሰናሰል ተገልጋዮች ቀልጣፋና ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር በመተባበር የኢንተርኔት አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው አካባቢ የሚገኙ ጤና ተቋማት ጭምር ''በሄልዝ ኔት'' ለማስተሳሰር መሰረት እየጣለ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የዲጂታል ጤና አገልግሎቱም የበሽታ መከላከልና አክሞ ማዳን አቅሞችን በማጎልበት ረገድ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የዲጂታል ጤና አገልግሎቶችን ተደራሽነት ለማስፋት በተከናወኑ ተግባራትም 40 ሶፍትዌሮችን በማልማት ተገልጋዮች የጤና መረጃና አገልግሎት እንዲያገኙና መረጃን በስፋት እንዲሰንዱ እየተደረገ መሆኑን አንሰተዋል።

በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የጤና ተቋማትን አገልግሎት ወረቀት አልባ የሚያደርግ ወሳኝ አቅም እየተፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል።

በቀጣይም በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሥርዓት የጤና ምኅዳሩን በዲጂታላይዜሽን የአሰራር ሥርዓት በማሳለጥ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026