🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባዋ በመልዕክታቸው፤ ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው ብለዋል።
9ኛው አዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ ዛሬ መጀመሩንም አስታውቀዋል።
የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ፣ ፈጣን፣ ግልፅ እና ተደራሽ ለማድረግ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ስራ በ2018 ዓ.ም በሁሉም ክፍለ ከተሞች ስራ ለማስጀመር ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

ለህዝቡ ቃል በተገባው መሰረትም የዛሬውን ጨምሮ ዘጠኝ ማዕከላትን ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ጠቁመዋል።
ይህ አሰራር የአገልግሎት እንግልትን፣ ጉቦ የመጠየቅ ችግርን ለመቅረፍ፣ ተጠያቂነትን እና የህዝብን በክብር የመገልገል መብት ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ነው ያብራሩት።
ህዝቡ ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜውንና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል ለማድረግ የታቀደውን ግብ በማሳካት የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ከንቲባዋ ገልጸዋል።
በየካ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ አዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ላደረጉት አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026