የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያና ዩናይትድ ኪንግደም ታሪካዊ ግንኙነት ወደላቀ ስትራቴጂክ አጋርነት እየተሸጋገረ ነው 

Jun 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያና ዩናይትድ ኪንግደም ታሪካዊ ግንኙነት ወደላቀ ስትራቴጂክ የዲፕሎማሲ አጋርነት እየተሸጋገረ መሆኑን በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን ገለጹ።

በኢትዮጵያ እና እንግሊዝ መካከል ያለው ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማሳደግ የተዘጋጀው የኢትዮ-እንግሊዝ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም 2026 በለንደን ከተማ ተካሂዷል።


በዩናይትድ-ኪንግደም የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን በዚሁ ጊዜ፤ ኢትዮጵያና እንግሊዝ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ዘመናትን የተሻገር ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ወዳጅ ሀገራት ናቸው ብለዋል።

የሀገራቱ መልካም ግንኙነትም የንግድና ኢንቨስትመንት የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ትብብርን በማሳደግ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ጭምር እያጠናከረ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በአሁኑ ወቅትም የኢትዮጵያና ዩናይትድ ኪንግደም ታሪካዊ ግንኙነት ወደላቀ ስትራቴጂክ የዲፕሎማሲ አጋርነት እየተሸጋገረ መሆኑን ተናግረዋል።

የሀገራቱ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረምም የኢኮኖሚክ ዲፕሎማሲ አጋርነትን ለማጎልበት ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የብዝኅ ዘርፍ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙ ለሀገራቱ ሁለንተናዊ የዲፕሎማሲ ትብብር አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩንም አንስተዋል።

በቀጣይም የሀገራቱን ሁለንተናዊ የዲፕሎማሲ ትብብር የበለጠ በማጠናከር የጋራ ተጠቃሚነትን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ ኤምባሲም የሁለቱን ሀገራት የንግድ፣ የኢንቨስትመንትን፣ የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ትብብር ወደ ላቀ ስትራቴጂክ አጋርነት ለማሸጋገር በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በፎረሙ ላይ የሀገራቱ የፖሊሲ አውጪ ሙያተኞች፣ ባለሃብቶችና የተለያዩ ተቋማት ጋር የሃሳብ ልውውጦች መደረጋቸው ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026