የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮጵያ ቀጣናዊ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች ነው

Jun 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ ወሳኝ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ ገለጹ።

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንትና የጂኦፖለቲካዊ ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ ያለመ "ሂሊ ዲያሎግ-አፍሪካ ኤዲሽን" የምክክር መድረክ ተካሂዷል።


የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ በመድረኩ፤ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ውጤታማ ስራ እያከናወነች ነው ብለዋል።

በዚህም የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን በኤሌክትሪክ ኃይል፣ በመንገድና በመሳሰሉት መሰረተ ልማቶች በማስተሳሰር የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጥ ገንቢ ሚና እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ እስከ ታንዛኒያ ድረስ የኤሌክትሪክ መስመር በመዘርጋት የምትሰራው ውጤታማ የልማት ሥራም አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች መሆኗን እንደሚያሳይ ተናግረዋል።

የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063ን ዕውን ለማድረግም አባል ሀገራት የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶችን መዘርጋት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊና ቀጣናዊ የመሰረተ ልማት ውጤቶችም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ለዲጂታል ኢኮኖሚ የተሰጠው ትኩረትም ንግድና ኢንቨስትመንትን በማሳለጥ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሃብቶች ጨምሮ ለውጭ አልሚዎች አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩን አስረድተዋል።

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የስትራቴጂክ ጥናትና ምርምር ማዕከል ኢኮኖሚስትና ተመራማሪ መሐመድ አል አባቢ በበኩላቸው፤ አፍሪካ በሁሉም መስክ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ስትራቴጂክ አጋር ናት ብለዋል።

በዚህም በምግብ ዋስትና፣ በታዳሽ ኃይልና ቁልፍ መሰረተ ልማት ግንባታ ዘርፍ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ ትብብር በመፍጠር እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026