የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ ህዝቡ ሲያቀርባቸው የነበሩ የልማት ጥያቄዎችን የፈቱ ፕሮጀክቶች በጥራት ተገንብተው ለአገልግሎት እየበቁ ነው

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆለታ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ህዝቡ ለረጅም ጊዜ ሲያቀርባቸው የነበሩ የልማት ጥያቄዎችን የፈቱ ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት ተገንብተው ለአገልግሎት እየበቁ መሆኑን የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ አስታወቁ።

በሆለታ ከተማ ዛሬ ከ700 ሚሊየን 413 ሺህ ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።


በከተማው ለአገልግሎት ከበቁ ፕሮጀክቶች መካከል የከተማ አስተዳደሩ ባለ 5 ወለል ህንፃ፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የይግባኝ ሰሚ ባህላዊ ፍርድ ቤት፣ የዶሮ እርባታ ክላስተር ማዕከል፣ የኮሪደር ልማት እና የጎጆ ኢንዱስትሪዎች መሆናቸው ተገልጿል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ እንደተናገሩት በክልሉ ከለውጡ ወዲህ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና ለረጅም ጊዜ ሲያቀርባቸው የነበሩ የልማት ጥያቄዎችን የፈቱ ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት ተገንብተው ለአገልግሎት እየበቁ ነው።


በተለይም ከተሞችን ለኑሮ ምቹ እንዲሁም የምርትና ምርታማነት ማዕከል ማድረግ፣ ቀልጣፋ፣ ፍትሐዊና ጥራት ያለው የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ስፍራ እየሆኑ ነው ብለዋል።

የሆለታ ከተማ በአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት የምትገኝና ረጅም ዕድሜ ያላት ብትሆንም፣ ቀደም ሲል በሚፈለገው ደረጃ ያልለማች ከተማ ነበረች ብለዋል።

ከለውጡ ወዲህ ግን በከተማዋ እየተከናወነ ባለው ሥራ ከተማዋ ለኑሮ ምቹ፣ የምርታማነት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን ገልጸዋል።

አዲሱ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከል ዜጎች የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የመንግሥት ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ እንዲያገኙ የሚያስችል ሲሆን፣ በማዕከሉ የተመደቡ ባለሙያዎችም የተጣለባቸውን አደራ በታማኝነት እንዲወጡ አሳስበዋል።

የሆለታ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ እሸቱ በቀለ በበኩላቸው፤ ዛሬ የተመረቁት ፕሮጀክቶች የከተማዋን የልማት ዕቅድ ከማሳካት ባለፉት ዓመታት ከተከናወኑት ሰፊ ሥራዎች መካከል ትልቅ ውጤት ናቸው ብለዋል።


በተለይም በ541 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው ባለ አምስት ወለል የከተማ አስተዳደር ሕንፃ የቢሮዎችን እጥረት በመቅረፍና ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ያስችላል ብለዋል።

ይህ መዋቅር የአገልግሎት ፈላጊዎችን እንግልት በማስቀረትና አላስፈላጊ ወጪን እንደሚያስቀር አብራርተዋል።

ከንቲባው አክለውም እነዚህ ፕሮጀክቶች የሥራ ዕድልን ለማስፋፋትና የማህበረሰቡን ኑሮ ለማሻሻል ጠንካራ መሠረት መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ማህበረሰቡ በከፍተኛ የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት የተገነቡትን ንብረቶች በአግባቡ ጠብቆ በመጠቀም ለልማቱ ቀጣይነት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026