የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የመሬት አካውንት መግለጫና የተፈጥሮ ካፒታል አካውንት ፍኖተ-ካርታ ይፋ ሆነ

Jul 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለው፣ አካታችና የማይበገር ዕድገት ለማስመዝገብ ለምታደርገው ጥረት ጠቃሚ መሰረት ሆኖ የሚያገለግለው የመሬት አካውንት መግለጫና የተፈጥሮ ካፒታል አካውንት ፍኖተ-ካርታ ይፋ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለጸ።

ሚኒስቴሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ዕትም የመሬት አካውንት መግለጫ ሪፖርት እና የተፈጥሮ ካፒታል አካውንት ፍኖተ-ካርታን ይፋ የማድረጊያ መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል።

በዚህ ይፋዊ መድረክ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍስሃፅዮን፣ የዓለም ባንክ የኦፕሬሽን ማናጀር ጁልያን ቪክቶር እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍሰሃፅዮን በመድረኩ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፤ ይፋ የሆኑት ሰነዶች ሀገራዊ የጋራ ራዕይን እውን ለማድረግ ትልቅ አቅም አላቸው።

በተለይም በመረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ ለመቅረጽ፣ የተፈጥሮ ሀብቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል፣ ቀጣይነት ያለው ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት በጋራ ለመስራት ያለንን ቁርጠኝነት የምናሳይበት ነው ብለዋል።


እነዚህ ሰነዶች ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት በተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች የተዘጋጁ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ይህም የላቀ የትብብር ውጤት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

ሰነዶቹ የተዘጋጁት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር በሚመራው ስቲሪንግ ኮሚቴ፣ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ተቋማት የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እንደሆነም አክለዋል።

ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በአህጉሪቱ ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባት የቻለች ብሎም የሚጨበጥ ስኬት ያስመዘገበች ሀገር መሆኗንም ጠቅሰዋል፡፡

ይህ ያስመዘገበችው ጠንካራ የኢኮኖሚ ዕድገትም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ህይወት በተጨባጭ መለወጡን ጠቁመዋል።

ለዚህ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ስኬት ለመሰረተ ልማት ግንባታ፣ ለጤና እና ለትምህርት የተሰጠው ከፍተኛ ትኩረትና በሌሎችም የተደረገው ኢንቨስትመንት ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷልም ብለዋል።

ቀጣይነት ያለውን ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የተፈጥሮ ሀብቶችን የመጠበቅ፣ የመንከባከብና የማልማት ተግባራትም በተሳካ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026