🔇Unmute
ሆሳዕና፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን ክህሎት በማሳደግ የሥራ ዕድል ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ማገዙን የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ገለፀ።
የቢሮው ሀላፊ ሰላሙ አማዶ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ የ5 ሚሊየን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን የቴክኖሎጂ ክህሎትና ተወዳዳሪነት በማሳደግ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እያስቻለ ነው።
ወጣቶቹም በስልጠናው ራሳቸውን በማብቃት ከሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ካሉ ካምፓኒዎች ጋር ተቀናጅተው በመስራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ ገቢያቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን አስረድተዋል።
በስልጠናው የብቃት ማረጋገጫ ያገኙ ወጣቶችን ከገበያው ጋር በማስተሳሰር ተጠቃሚ መሆናቸውንም አንስተዋል።
በሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደው ወደ ሥራ ከተቀላቀሉ ወጣቶች መካከል ጫኪሶ ወልዴ አንዱ ሲሆን በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ያገኘው እውቀት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንደሚያደርገው ተናግሯል።
ይህም ከሥራ ጠባቂነት ይልቅ የራሱን ስራ በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ አቅሙን እንሚያጠናክርለት ገልጿል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ ለዲጂታል ቴክኖሎጂ የተሰጠው ትኩረት የወጣቶችን ሥራ ፈጣሪነትና ተወዳዳሪነት በማረጋገጡ ሌሎችም የእሱን ተሞክሮ እንዲወስዱ መክሯል።
ሌላኛው ወጣት አብይ ላቀው በበኩሉ በኢትዮ ኮደርስ መርሃ ግብር የወሰደው ስልጠና በዘርፉ የነበረውን እውቀት ይበልጥ ለማሳደግ እንዳስቻለው ተናግሯል።
ስልጠናው በኦን ላይን ገቢ በማመንጨት ተጠቃሚ መሆን የሚያስችለውን በቂ እውቀት ለማግኘት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረለትም ጠቁሟል።
በዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚሰሩ ሥራዎችን በቤቱ ሆኖ በኦን ላይን በመስራት ገቢ ማግኘት መጀመሩን ነው የገለጸው።
ባለፉት ሁለት ዓመታት በክልሉ ከ242ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን ተከታትለው የእውቅና የምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026