የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በከተማዋ በሚከናወኑ የልማት ስራዎች የታማኝ ግብር ከፋዮች ሚና የጎላ ነው- ከንቲባ ጥራቱ በየነ

Jul 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

‎ሀዋሳ ሰኔ 29/2018 (ኢዜአ)፦ በሀዋሳ ከተማ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሚከናወኑ የልማት ስራዎች የታማኝ ግብር ከፋዮች ሚና የጎላ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለፁ።

‎የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለሥልጣን ዋና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ2017/18 ግብር ዘመን ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የዕውቅናና ሽልማት እንዲሁም የ2018/19 ግብር ዘመን የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል።


በመድረኩ ላይ የተገኙት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ በከተማዋ ከግብር ከፋዮች በሚሰበሰብ ገቢ የነዋሪዎችን ፍላጎት የሚያሟሉ ለትውልድ የሚሻገሩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።

ታማኝ ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር በአግባቡ በመክፈል በከተማዋ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡


ከንቲባ ጥራቱ አክለውም የከተማዋ ግብር ከፋዮች ከመደበኛ የግብር ግዴታቸው ባሻገር በከተማዋ ለሚከናወነው የኮሪደርና ሐይቅ ዳርቻ ልማት ድጋፍ በማድረግም አሻራቸውን እያኖሩ እንደሚገኙ አውስተዋል።‎

በከተማዋ የሚገኙ ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በሚከናወነው የቀጣዩ ግብር ዘመን ገቢ አሰባሰብ ላይም ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።


የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለሥልጣን ዋና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መልኩ ማርቆስ በበኩላቸው በከተማዋ ገቢን አሟጦ ከመሰብሰብ አኳያ የነበሩ ክፍተቶችን በመሙላት በየዓመቱ እያደገ የሚሄድ መሻሻል እየተመዘገበ መሆኑን ገልፀዋል።‎

በ2017/18 ግብር ዘመን 6 ነጥብ 4 ቢሊዮብ ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከእቅድ በላይ 7 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን አመልክተዋል ።

ለዚህ ስኬት የሚጠበቅባቸውን ግዴታ በወቅቱና በአግባቡ የሚከፍሉ ግብር ከፋዮች የጎላ ድርሻ መወጣታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

የስነ ስርአቱ ዓላማ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮችን ለማበረታታትና ሌሎችም የነርሱን አርአያ እንዲከተሉ መነሳሳት ለመፍጠር መሆኑን ጠቁመዋል።


ዕውቅናና ሽልማት ከተበረከተላቸው ግብር ከፋዮች መካከል በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩት አቶ ተስፋዬ ፀጋዬ በተሰጣቸው ዕውቅናና ሽልማት መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡

በቀጣይ ጊዜያት በላቀ ደረጃ በታማኝነትና በወቅቱ ግብራቸውን በመክፈል በከተማዋ በሚከናወነው የልማት ሥራ ላይ የላቀ አስተዋፅዖ ለማድረግ ያነሳሳቸው መሆኑን አመልክተዋል፡፡

በአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ላይ የተሰማሩት አቶ አብርሃም ኮላቶ በበኩላቸው ከግብር ከፋዮች በሚሰበሰብ ገቢ ለትውልድ የሚሸጋገሩ መሰረተ ልማቶች የሚገነቡ በመሆኑ በግብር ከፋይነታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

በስነ ስርአቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩና የክፍለ ከተሞች የሥራ ኃላፊዎች፣ ግብር ከፋዮችና ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026