የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና በማጎልበት ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና በማጎልበት ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።

የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) አባል አገራት የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና ላይ ያተኮረ የሁለት ቀናት አውደ ጥናት እየተካሄደ ይገኛል።

በአውደ ጥናቱ መክፈቻ ላይ በግብርና ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ ዜና ሀብተወልድ እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና ለማስፋፋት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል።

የመስኖ ስንዴ ልማት፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የአፈር መሸርሸርን መከላከልና ጤንነትን የመጠበቅ፣ የእንስሳት ምርታማነትን የማሻሻያና ሌሎች ስራዎችን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ግብርና ለማጎልበት የተገኙ ውጤቶች ለኢጋድ አባል ሀገራት ተሞክሮ የሚውሉ መሆናቸውን አመልክተው፤ በቀጣናው የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል የግብርና ልህቀት ማዕከል ለማቋቋም ግብዓት እንደሚሆን አንስተዋል።

የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም ስራዎች በአንድ ሀገር ብቻ የሚከናወን ሳይሆን የአገራት ቅንጅት የሚያስፈልግ በመሆኑ ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) ጋር የሚከናወኑ ተግባራትን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢጋድ አባል ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ከመቋቋም አኳያ ያሉበት ደረጃ ላይ ያተኮረ ጥናት መካሄዱን ገልጸዋል።

በአውደ ጥናቱ ውይይት የሚቀርበው ጥናት የአባል አገራትን የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና የልህቀት ማዕከላትን ለማቋቋም፣ ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርናን የመቋቋም አቅምን ለመገንባት ወሳኝ ነው ብለዋል።

በምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) የግብርና እና አካባቢ ጥበቃ ዳይሬክተር ዳሄር ኤልሚ በመወከል የኢጋድ የፖሊሲና የምግብ ዋስትና ኤክስፐርት ሲልቪያ ሄንጋ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የአየር ንብረት ለውጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አምራች አርሶ አደሮችን እየጎዳ ይገኛል ።

የሙቀት መጠን መጨመር፣ ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋዎች፣ የመሬት መራቆት፣ የምግብ ዋስትናና ሌሎች ችግሮች የኢኮኖሚ እድገትን እና ዘላቂ ልማትን እያደናቀፉ ይገኛሉ ብለዋል።

በመሆኑም፣ የመቋቋም አቅም ያለው ግብርና፣ ምርታማ እና ዘላቂ የምግብ ሥርዓትን ለመገንባት የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና ወሳኝ መሆኑን ነው የገለጹት።

በሳይንስ፣ በማስረጃ እና ውጤታማ በሆኑ የእውቀት ሽግግር ላይ የተመሰረቱ ፈጠራ የታከለባቸው እና የተቀናጁ ቀጣናዊ ምላሾችን ይሻሉ ብለዋል።

አውደ ጥናቱ የኢጋድ አባል አገራት የምግብ ሥርዓቶች የመቋቋም አቅም ፕሮግራም ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ ነው፤ የቀጣናውን ተጨባጭ ሁኔታዎች በትክክል የሚያንፀባርቅ እና ወደ ተግባር ሊቀየሩ የሚችሉ ምክረ-ሃሳቦች እንዲሁም ቴክኒካዊ እውቀት ለማጎልበት ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026