የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የግብርና ሥራን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው

Jul 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ፤ ሐምሌ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ሥራን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በወላይታ ዞን ዱጉና ፋንጎ ወረዳ ከ21 ሚሊዮን 500 ሺህ ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባውን የብላቴ ኤታ መስኖ አውታር ለአገልግሎት አብቅቷል።


በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ አቶ ኤካል ነትር እንደገለጹት፤ በክልሉ የመስኖ አውታሮችን በማስፋፋት የአርሶ አደሩን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።

ይህም አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ በዓመት ሁለትና ሦስት ጊዜ በማምረት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እያገዘ ይገኛል ብለዋል።


ዛሬ የተመረቀው ፕሮጀክትም ከ1 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት የማልማት አቅም ያለው ሲሆን፤ ከ1 ሺህ 200 በላይ አርሶ አደሮችን ቀጥተኛ ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ኃላፊው አብራርተዋል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በበኩላቸው፤ በዞኑ የሚገኙ አርሶ አደሮች ያሉትን የውኃ አማራጮች በመጠቀም በመስኖ እንዲያለሙ በተደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።


ሥራው አርሶ አደሩን ከተረጂነት በማላቀቅ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ ትልቅ አቅም መፍጠሩን ጠቅሰዋል፡፡

የዱጉና ፋንጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘካሪያስ ዎንታሞ በበኩላቸው፤ በወረዳው ሰፊ ሊለማ የሚችል የእርሻ መሬት መኖሩን ጠቅሰው፣ አርሶ አደሮች በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ በማልማት ወደተሻለ የኑሮ ደረጃ እየተሸጋገሩ መሆኑን ተናግረዋል።


ዛሬ የተመረቀው የመስኖ ፕሮጀክትም የሦስት ቀበሌ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ኢዜአ ያነጋገራቸው የብላቴ ኤታ እና የፓንጎ ቢጆ ቀበሌ አርሶ አደሮች፤ ቀደም ሲል የዝናብ ወቅትን ብቻ በመጠበቅ በዓመት አንድ ጊዜ ያመርቱ እንደነበርና ኑሯቸውም ከእጅ ወደ አፍ እንደነበር አስታውሰዋል።

ከዚህ በኋላ በመስኖው በመታገዝ ሰብል እንዲሁም አትክልትና ፍራፍሬዎችን በማምረት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026