የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኩታገጠም እርሻ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ የገጠር ትራንስፎርሜሽንን እያፋጠነ ነው

Jul 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 6/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የኩታገጠም የግብርና እርሻ ሥርዓት የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ የገጠር ትራንስፎርሜሽንን እያፋጠነ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር) ገለጹ።

ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥የገጠር ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂው የአርሶ አደሩን የግብርና ሥርዓት በማዘመን፣ዘላቂ የምርታማነት ምኅዳር በመፍጠር ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነት አድማስ እየሰፋ መምጣቱ ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥና ለገጠር ትራንስፎርሜሽን መፋጠን ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም አንስተዋል።


ይህም የግብርናውን ዘርፍ ከባህላዊ አሠራር በማላቀቅ አዳዲስ አማራጮችን በመፍጠርና ሜካናይዜሽንን በማስፋፋት የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነትና የኑሮ ደረጃ ላይ ከፍተኛ መሻሻል እያመጣ መሆኑን አስረድተዋል።

የኩታገጠም የግብርና አሠራርና የሜካናይዜሽን ሥርዓት መተግበር የሰብል ምርታማነትን በብዛትና በጥራት ለማሳደግ ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

ቀደም ሲል በአመት አንድ ጊዜ ብቻ ይታረስ የነበረው መሬት አሁን ላይ በበጋ መስኖና በተለያዩ የምርታማነት ወቅቶች ታግዞ ምርታማነቱን ማሳደግ እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣የሀገሪቱን የምግብ ፍጆታ በማሟላት አልፎም ለውጭ ገበያ መቅረብ የሚችልበትን አስተማማኝ መዋቅራዊ የስኬት ሽግግር ማስመዝገቡን አብራርተዋል።


የኩታገጠም ዘመናዊ አስተራረስ ዘዴም የሚታረስን መሬት በማስፋትና አርሶ አደሩ ከራሱ ፍጆታ አልፎ ለገበያ የሚያቀርብበትን አቅም በመፍጠር የገጠር ኢኮኖሚን እያነቃቃ ነው ብለዋል።

ይህ አሠራር ለግብርና ምርቶች እሴት በመጨመር ረገድ በሚደረጉ ጥረቶች ታግዞ የገጠር ሽግግርን ከማፋጠን ባሻገር የሥራ ዕድል በመፍጠርና ለኢንዱስትሪ ልማት ግብዓት በማቅረብ ረገድ አመርቂ ውጤቶችን እያስመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል።


የኩታገጠም የግብርና አስተራረስና የሜካናይዜሽን ሥርዓት መዘርጋት የኢትዮጵያን የግብርና ዘርፍ ወደ ዘመናዊ ምዕራፍ በማሸጋገር የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና የዜጎችን ተጠቃሚነት የማሳደግ ጉዞን እያፋጠነ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026