የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ለምርምር ስራዎቹ ተደራሽነት ከኢዜአ ጋር ያለውን አጋርነት አጠናክሮ ይቀጥላል

Jul 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ) ፦ የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ በምርምርና ሃገር በቀል እውቀቶች የሚያከናውናቸውን ስራዎች ተደራሽነት ለማስፋት ከኢዜአ ጋር ያለውን አጋርነት አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተመስገን ደበሎ (ዶ/ር) ገለጹ።

የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በምርምር ስራዎችና ሀገር በቀል እውቀቶች ተደራሽነት ላይ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።


የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት በስምምነቱ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢዜአ ሰፊ ተደራሽነት ያለው ተጽዕኖ ፈጣሪ የመገናኛ ብዙሃን ተቋም ስለሆነ ስምምነቱ ለዩኒቨርሲቲው ትልቅ ዋጋ አለው።

ዩኒቨርሲቲው ከሶስተኛው ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል እንደሚመደብ ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛልም ብለዋል።

በተለይም በግብርና፣ በማዕድን እና ከገዳ ስርዓት ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ሀገር በቀል እውቀቶች ከዘመናዊ የትምህርት ስርዓት ጋር በማቀናጀት ለሀገር እድገት የሚጠበቅበትን እየተወጣ መሆኑንም አስረድተዋል።

ስምምነቱ ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን ተግባራት በሀገር አቀፍ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት ለማስተዋወቅ፣ እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥር ዶክተር ተመስገን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው ከ85 ዓመታት በላይ የካበተ ልምድ ያለው ኢዜአ፤ በለውጥ ሂደት ላይ እንደሚገኝ አስታውሰው ሁለቱ ተቋማት የፈጸሙት ስምምነትን የያዟቸውን የጋራ ግቦች ለማሳካት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ አካባቢ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችና ሀገር በቀል እውቀቶችን በአህጉራዊ ደረጃ ለማስተዋወቅ ኢዜአ በዘርፉ ካለው የላቀ አቅም አኳያ ተመራጭ አጋር መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ስምምነቱ በመደመር እሳቤ ሀገር በቀል እውቀትን ተጠቅሞ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ለተያዘው ግብ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው አስረድተዋል።

ኢዜአ ከዜና ስራዎች ባሻገር በዓለም አቀፍ ምርምር፣ በዶክመንተሪ እና በተለያዩ ፕሮግራሞች ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው ዩኒቨርሲቲው በአፍሪካ ደረጃ ተጠቃሽ ተቋም ለመሆን ለሚያደርገው ጥረት አጋዥ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026