🔇Unmute
ነገሌ ቦረና፤ሐምሌ 9 /2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ቦረና ዞን የተሻሻለ የግብርና አሰራር ተግባራዊ በመደረጉ ምርታማነትን ለማሳደግ እያገዘ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡
በክልሉ በልግ አብቃይ ከሆኑ አካባቢዎች መካከል አንዱ የሆነው የምስራቅ ቦረና ዞን ከመጋቢት አጋማሽ እስከ ሚያዝያ የበልግ ዝናብና የዘር፣ ከሐምሌ እስከ ነሐሴ አጋማሽ ደግሞ የምርት መሰብሰቢያ ወቅት ነው፡፡
በጽሕፈት ቤቱ የአዝርእት ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ሊበን ቦሩ እንደገለጹት፤ በዞኑ የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ ከለማው ከ176 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ምርት እየተሰበሰበ ነው።

በዞኑ በበልግ አዝመራ ከለሙት የሰብል ዓይነቶች መካከል ስንዴ፣ ጤፍ፣ በቆሎና ቦለቄ ዋና ዋናዎቹ መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡
የበልግ አዝመራውን ምርታማነት ለማሳደግም ከ70 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉንም ገልጸዋል፡፡
በዞኑ የበልግ አዝመራ 162 ሺህ 804 ከፊል አርብቶ አደሮችና አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ጠቅሰው፣ ይህም የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዞኑ በበልግ አዝመራ ከለማው ሰብልም በ61 ሺህ ሄክታሩ በስንዴ ሰብል የለማ መሆኑንና ከዚህም መሬት 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ብለዋል፡፡
የስንዴ ልማቱን ለማሳደግ የትራክተር፣ የኩታ ገጠምና የመስመር አዘራር ዘዴ እንዲሁም ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋላቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ወጪና ጊዜ በመቆጠብ የምርት አሰባሰብ ሂደቱን ለማፋጠንም ኮምባይነሮች ሥራ ላይ መዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡

በዞኑ ሊበን ወረዳ የሜኤሳ ዳሎሬ ቀበሌ ነዋሪ አቶ በዳዳ ጀልዴሳ በአካባቢያቸው የሚስተዋለውን ዝናብ አጠር የአየር ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ እርጥበትን በመጠቀም በዘንድሮ በበልግ አዝመራ 3 ሄክታር መሬት ለመጀመሪያ ጊዜ በተሻሻለ የግብርና አሰራር የስንዴ ምርጥ ዘር ማልማታቸውን ገልጸዋል፡፡
መሬታቸውን በትራክተር አርሰው፣ ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ በመጠቀምና ሰብሉን በኮምባይነር እየሰበሰቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
የዚሁ ወረዳ ነዋሪ አቶ አብጉዶ ዋሪዮ፤ በተሻሻለ የግብርና አሰራር ያለሙት ሰብል ውጤታማ እያደረጋቸው እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
መንግስት ለስንዴ ሰብል ልማት የሰጠው ልዩ ትኩረት ለሥራቸው መሳካትና የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እንዳገዛቸውም ጠቁመዋል፡፡
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026