የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን ቀድሞ በመከላከል አቅም ገንብቶ በማየታችን ኮርተናል

Jul 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን መከላከልና ለወረርሽኞች የተቀናጀና ሳይንሳዊ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም በመገንባቱ ኩራት እንደተሰማቸው ተቋሙን ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ ሠራተኞችና የቀድሞ አመራር ገለጹ።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በተለያዩ ኹነቶች ያከበረ ሲሆን፣ ተቋሙን ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅና ተሰጥቷቸዋል።


እውቅና ከተሰጣቸው መካከል ተቋሙን ለ25 ዓመታት ከተመራማሪነት እስከ ዋና ዳይሬክተርነት ያገለገሉት ዶክተር አምሃ ከበደ አንዱ ናቸው።

የቀድሞው ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አምሃ በተለያየ የሙያና የኃላፊነት እርከን በማገልገል የተቋሙ የምዕተ ዓመት ታሪክ ላይ አስተዋፅኦ ማበርከታቸው እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።

ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ዓመታት ባካሄዳቸው መዋቅራዊ ሪፎርሞች ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን ቀድሞ የመከላከል አቅሙን በማሳደጉ ኩራት እንደተሰማቸው ገልፀዋል።

ኮቪድ-19ን ጨምሮ በቅርቡ የተከሰቱትን ኤምፖክስና ማርበርግ የመሰሉ ወረርሽኞችን በተቀናጀ፣ ፈጣንና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በመመከት በኩል ያስመዘገበው ስኬት ተቋሙ የደረሰበት የላቀ የመከላከል አቅም ማሳያ መሆኑንም ጠቁመዋል።


በተቋሙ ለ44 ዓመታት በማገልገል የሕይወት ዘመን ተሸላሚ የሆኑት ጎንፋ አያና ተቋሙን ባገለገሉባቸው ዓመታት ኢንስቲትዩቱ የስምና አደረጃጀት ለውጥ በማድረግ በሕብረተሰብ ጤና ላይ ጉልህ ድርሻ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።

ኢንስቲትዩቱ አሁን ላይ የቴክኖሎጂና የባለሙያ አቅሙን በማሳደግ ተወዳዳሪ ተቋም መሆን መቻሉን ተናግረዋል።

ለበርካታ ዓመታት በማገልገል እውቅና በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው፣ የአሁኑ ትውልድም ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ሀገሩን በተሻለ መንገድ እንዲያገለግል አስገንዝበዋል።

#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026