የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን ቀድሞ በመከላከል አቅም ገንብቶ በማየታችን ኮርተናል

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን መከላከልና ለወረርሽኞች የተቀናጀና ሳይንሳዊ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም በመገንባቱ ኩራት እንደተሰማቸው ተቋሙን ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ ሠራተኞችና የቀድሞ አመራር ገለጹ።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በተለያዩ ኹነቶች ያከበረ ሲሆን፣ ተቋሙን ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ አመራሮችና ሠራተኞች እውቅና ተሰጥቷቸዋል።


እውቅና ከተሰጣቸው መካከል ተቋሙን ለ25 ዓመታት ከተመራማሪነት እስከ ዋና ዳይሬክተርነት ያገለገሉት ዶክተር አምሃ ከበደ አንዱ ናቸው።

የቀድሞው ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አምሃ በተለያየ የሙያና የኃላፊነት እርከን በማገልገል የተቋሙ የምዕተ ዓመት ታሪክ ላይ አስተዋፅኦ ማበርከታቸው እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።

ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ዓመታት ባካሄዳቸው መዋቅራዊ ሪፎርሞች ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን ቀድሞ የመከላከል አቅሙን በማሳደጉ ኩራት እንደተሰማቸው ገልፀዋል።

ኮቪድ-19ን ጨምሮ በቅርቡ የተከሰቱትን ኤምፖክስና ማርበርግ የመሰሉ ወረርሽኞችን በተቀናጀ፣ ፈጣንና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በመመከት በኩል ያስመዘገበው ስኬት ተቋሙ የደረሰበት የላቀ የመከላከል አቅም ማሳያ መሆኑንም ጠቁመዋል።


በተቋሙ ለ44 ዓመታት በማገልገል የሕይወት ዘመን ተሸላሚ የሆኑት ጎንፋ አያና ተቋሙን ባገለገሉባቸው ዓመታት ኢንስቲትዩቱ የስምና አደረጃጀት ለውጥ በማድረግ በሕብረተሰብ ጤና ላይ ጉልህ ድርሻ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።

ኢንስቲትዩቱ አሁን ላይ የቴክኖሎጂና የባለሙያ አቅሙን በማሳደግ ተወዳዳሪ ተቋም መሆን መቻሉን ተናግረዋል።

ለበርካታ ዓመታት በማገልገል እውቅና በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው፣ የአሁኑ ትውልድም ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ሀገሩን በተሻለ መንገድ እንዲያገለግል አስገንዝበዋል።

#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...

Jul 16, 2026

ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...

Jul 7, 2026

የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው

ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Jul 1, 2026

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...

Jun 30, 2026