🔇Unmute
ሀረር፤ ሐምሌ 11 /2018 (ኢዜአ)፡- የገቢ አማራጮችን በማስፋትና ያሉትን አቅሞች በአግባቡ በመጠቀም ለላቀ የልማት ስኬት ልንዘጋጅ ይገባል ሲሉ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
የሐረሪ ክልል የ2018 የገቢ እቅድ ማጠቃለያና የ2019 በጀት አመት የገቢ ንቅናቄ ማስጀመሪያ መድረክ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ በክልሉ የገቢ አማራጮችን በማስፋትና ያሉትን አቅሞች በአግባቡ በመጠቀም ለላቀ የልማት ስኬት ልንዘጋጅ ይገባል ብለዋል።
በክልሉ የሚሰበሰበው ገቢ ካለፉት ዓመታት አንጻር የተሻለ ቢሆንም ገና ብዙ መስራት ይጠበቅብናል ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ ግብርን በታማኝነትና በቅንነት የመክፈል ባህል ማደግ አለበት ብለዋል።

በታማኝነት የሚጠበቅባቸውን ግብር ሲከፍሉ የነበሩና ለስኬቱ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት የተወጡ ባለድርሻ አከላት አስተዋጽዎ ከፍተኛ እንደነበር አስታውሰዋል።
በ2019 በጀት ዓመት የተያዘውን እቅድ ስኬታማ ለማድረግ ዘመናዊ አሰራሮችን በማጎልበት፣ ህገ ወጥ ንግድና ታክስ ስወራን በመከላከል ለተሻለ የልማት ስኬት መትጋት አለብን ብለዋል።
የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ያሲን አብዱላሂ ፤ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የታቀዱ የልማት ስራዎችን ለማሳካት ጥረት መደረጉን አንስተው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።

በ2018 በጀት ዓመት ከተለያዩ ርዕሶች ከ4 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የእቅዱን 99 በመቶ ማሳካት ስለመቻሉ አንስተው በተያዘው በጀት ዓመትም እቅዱን ለማሳካት በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ በክልሉ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ካልሆነ ታክስ፣ ከመዘጋጃ ቤት አገልግሎትና ከሌሎች ከ6 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።
በመድረኩ ላይ የክልሉ አመራር አካላት ግብር ከፋዮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን ለታማኝ ግብር ከፋዮችም እውቅና ተሰጥቷል።
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...
Jul 16, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...
Jul 7, 2026
ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Jul 1, 2026
አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...
Jun 30, 2026