የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የገቢ አማራጮችን በማስፋትና ያሉትን አቅሞች በአግባቡ በመጠቀም ለላቀ የልማት ስኬት መዘጋጀት አለብን - ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ

Jul 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀረር፤ ሐምሌ 11 /2018 (ኢዜአ)፡- የገቢ አማራጮችን በማስፋትና ያሉትን አቅሞች በአግባቡ በመጠቀም ለላቀ የልማት ስኬት ልንዘጋጅ ይገባል ሲሉ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።

የሐረሪ ክልል የ2018 የገቢ እቅድ ማጠቃለያና የ2019 በጀት አመት የገቢ ንቅናቄ ማስጀመሪያ መድረክ ተካሂዷል፡፡


በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፤ በክልሉ የገቢ አማራጮችን በማስፋትና ያሉትን አቅሞች በአግባቡ በመጠቀም ለላቀ የልማት ስኬት ልንዘጋጅ ይገባል ብለዋል።

በክልሉ የሚሰበሰበው ገቢ ካለፉት ዓመታት አንጻር የተሻለ ቢሆንም ገና ብዙ መስራት ይጠበቅብናል ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ ግብርን በታማኝነትና በቅንነት የመክፈል ባህል ማደግ አለበት ብለዋል።


በታማኝነት የሚጠበቅባቸውን ግብር ሲከፍሉ የነበሩና ለስኬቱ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት የተወጡ ባለድርሻ አከላት አስተዋጽዎ ከፍተኛ እንደነበር አስታውሰዋል።

በ2019 በጀት ዓመት የተያዘውን እቅድ ስኬታማ ለማድረግ ዘመናዊ አሰራሮችን በማጎልበት፣ ህገ ወጥ ንግድና ታክስ ስወራን በመከላከል ለተሻለ የልማት ስኬት መትጋት አለብን ብለዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ያሲን አብዱላሂ ፤ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የታቀዱ የልማት ስራዎችን ለማሳካት ጥረት መደረጉን አንስተው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።


በ2018 በጀት ዓመት ከተለያዩ ርዕሶች ከ4 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የእቅዱን 99 በመቶ ማሳካት ስለመቻሉ አንስተው በተያዘው በጀት ዓመትም እቅዱን ለማሳካት በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በክልሉ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ካልሆነ ታክስ፣ ከመዘጋጃ ቤት አገልግሎትና ከሌሎች ከ6 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

በመድረኩ ላይ የክልሉ አመራር አካላት ግብር ከፋዮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን ለታማኝ ግብር ከፋዮችም እውቅና ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026