የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ጨፌ ኦሮሚያ ለክልሉ መንግሥት የ2019 በጀት ዓመት ሥራ ማስፈጸሚያ 704 ቢሊዮን ብር በጀት አጸደቀ

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፣ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ጨፌ ኦሮሚያ ለተያዘው በጀት ዓመት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል 704 ቢሊዮን ብር በጀት በሙሉ ድምፅ አጸደቀ።

ጨፌ ኦሮሚያ በ6ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤው የዛሬ ውሎ የክልሉን መንግሥት የ2019 በጀት አጽድቋል።

የኦሮሚያ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶሎሳ ገደፋ የበጀት ዝርዝሩን ለጨፌው ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በጀቱ ከተረጂነት ለመውጣትና ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብና ስትራቴጂ ለማሳካት ያለመ ነው።

የበጀት ድልድሉም የልማት ፕሮግራሞችን መሠረት በማድረግና የክልሉን ዕድገት ለማፋጠን በሚያስችል መልኩ ተከናውኗል ብለዋል።

የልማት ዕቅዱን ውጤታማ ለማድረግ ከሁሉም የክልሉ ሴክተር ተቋማት ጋር ውይይት መደረጉን የጠቀሱት ኃላፊው፤ ትኩረት ለሚሹ ጉዳዮች በበጀት ድልድሉ ቅድሚያ መሰጠቱን ተናግረዋል።


በጀቱ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ76 በመቶ ጭማሪ ያለው ሲሆን፣ የበጀት ድልድሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ በተለይም በከተሞችና በወረዳዎች ለሚከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቷል ብለዋል።

በዚህም መሠረት ለጤና፣ ለትምህርት እና ለመንገድ መሠረተ ልማት አንዲሁም ለመስኖ እና ለንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ቅድሚያ ተሰጥቷል ነው ያሉት።

ይህ በጀት በከተሞችና በወረዳዎች መካከል ሊኖር የሚችለውን የመሠረተ ልማት ልዩነት ለማጥበብና በክልሉ ቆላማ አካባቢዎች የሚገኙ ሰፋፊ መሬቶችን ለማልማት የሚያስችሉ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ታሳቢ ማድረጉንም ኃላፊው ገልጸዋል።

ከተሞችና ወረዳዎች የሚሰጣቸውን በጀት ለማኅበራዊ መሠረተ ልማት ማዋል ላይ ትኩረት አድርገው መደልደል እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ማንኛውንም የገቢ ዓይነት ያለ ሕጋዊ ደረሰኝ መሰብሰብ የተከለከለና የሕግ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑንም አሳስበዋል።

የጨፌው አባላት በቀረበው የበጀት ቀመር ላይ በሰጡት አስተያየት፤ የበጀት ድልድሉ ከተረጂነት ለመውጣትና ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።

ሆኖም ከበጀት ድልድሉ ባለፈ፣ የካፒታል በጀትን ጨምሮ የተመደበው ሀብት ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል ጠንካራ ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...

Jul 16, 2026

ሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማን የኢንዱስትሪና የአገልግሎት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስ...

Jul 7, 2026

የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ጥገናን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው

ኮምቦልቻ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡- የአዋሽ-ኮምቦልቻ- ሃራ ገበያ ባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥገናን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Jul 1, 2026

ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ እና ጣሊያን የ70 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር ስምምነ...

Jun 30, 2026